በድሬዳዋ ሴቶች ጓዳ ተቀምጠው ዱቄት ከመጠበቅ ይልቅ የራሳቸውን ዱቄት ፋብሪካ ከፍተው እየሰሩ ይገኛሉ ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ተናገሩ
ሚኒስተሩ ይህንን የተናገሩት በዛሬው ዕለት ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ጋር በጋራ በመሆን 11 አምራች ኢንደስትሪዎችን ሲመርቁ ነው። ከተመረቁት ኢንደስትሪዎች መካከል “ባህር ዱቄት ፋብሪካ” አንዱ ሲሆን የፋብሪካው ባለቤት እና ስራ አስኪያጅም ማርያ ሳላ ይባላሉ። ባህር የዱቄት ፋብሪካ በ 37 ሚሊየን ብር ካታል እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ፋብሪካ ሲሆን ለ 21 ዜጎችም የስራ እድልን ፈጥሯል። የፋብሪካው…


