direcom

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል። የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የዐሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን…

Read More

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የ2019 በጀትን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ::

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ 1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ካሉበት ተግዳሮቶች እየተላቀቀና የኢኮኖሚው መሰረቶችም እየተጠናከሩ መጥተዋል፡፡ ማዕቀፉ በኢኮኖሚ ሪፎርሙ የተገኙ አበረታች ውጤቶችን ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲያስችልና…

Read More

ብልፅግና ፓርቲ የምርጫ አፈጻጸም ግምገማውን አጠናቀቀ::

ብልፅግና ፓርቲ በጅግጅጋ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በስኬት አጠናቋል። ​ ​የብልፅግና ፓርቲ የብሔራዊ የምርጫ አስተባባሪ ኮሚቴ፣ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች በተገኙበት በዚህ መድረክ ላይ የሚከተሉት አበይት ጉዳዮች ተገምግመዋል:: ​ፓርቲው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዕቅዱ መሠረት በቅድመ ምርጫ እና በምርጫው…

Read More

የኢትዮጵያ ስልታዊ ዲፕሎማሲ፦ ከውስጥ ጽናት እስከ ዓለም አቀፍ ከፍታ

ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው። ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው። ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ “የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ…

Read More

የኢትዮጵያ የምግብ ሥርዓት ሽግግር እና ኒዩትሪሽን ንቅናቄ በድሬዳዋ አስተዳደር በይፋ መተግበር መጀመሩ ተበሰረ::

​የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት (ATI) ከድሬዳዋ አስተዳደር ጋር በመተባበር ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር “የምግብ ሥርዓት ሽግግር ፍኖተ-ካርታ” ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አከናወነ። ይህ ፍኖተ-ካርታ በአስተዳደሩ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖረውን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርግና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር የሚያግዝ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል። ​የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዶ/ር ሰይፉ ታደሰ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደተናገሩት የፍኖተ-ካርታው ራዕይ በከተማም ሆነ…

Read More

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ ልዑክ ጅግጅጋ ገብቷል።

ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር እና ክብርት አዳነች አቤቤን ጨምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች የተካተቱበት ልዑክ ጅግጅጋ ከተማ ገራድ ዊልዋል አየር ማረፊያ ሲደርሱ የሶማሊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላለፈ::

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል። 1ኛ:- ካቢኔው በቀዳሚነት የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ፕላን ሥራዎች ላይ በመወያየት ውሳኔ አስተላልፏል። የከተማ ፕላን ሥራዎች የድሬዳዋን ፈጣን ዕድገት በስልታዊ መንገድ ለመምራት ከፍተኛ ሚና አላቸው። የመኖሪያና የንግድ ቀጠናዎችን በዘመናዊ አሠራር በመለየት ለቀጣይ መሠረተ ልማት፣ ለኢንቨስትመንት መስፋፋት እና ለከተማዋ ውበት ምቹና ዘላቂ መሠረት…

Read More

​የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጅሃር በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዛሬው ዕለት በግንባር ተገኝተው ድምፅ ሰጥተዋል።

ከንቲባው ድምፃቸውን የሰጡት በአስተዳደሩ ወረዳ 04 በሚገኘው ምርጫ ጣቢያ አንድ ነው። ​ከንቲባ ከድር ጁሃር ድምፅ በሰጡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ዜጎች በሕገ-መንግስቱ የተሰጣቸውን የመምረጥ መብት በአግባቡና በሃላፊነት ስሜት ሊጠቀሙበት እንደሚገባ አሳስበዋል። 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ስኬታማና ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ዝግጅት መደረጉን የገለጹት ከንቲባው፤ መላው ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ፓርቲ ለመምረጥና የአገሪቱን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ…

Read More