የኢትዮጵያ የምግብ ሥርዓት ሽግግር እና ኒዩትሪሽን ንቅናቄ በድሬዳዋ አስተዳደር በይፋ መተግበር መጀመሩ ተበሰረ::
የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት (ATI) ከድሬዳዋ አስተዳደር ጋር በመተባበር ለመጪዎቹ አምስት ዓመታት የሚተገበር “የምግብ ሥርዓት ሽግግር ፍኖተ-ካርታ” ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አከናወነ። ይህ ፍኖተ-ካርታ በአስተዳደሩ በከተማም ሆነ በገጠር የሚኖረውን የህብረተሰብ ክፍል ተጠቃሚ የሚያደርግና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር የሚያግዝ መሆኑ በመድረኩ ተገልጿል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ዶ/ር ሰይፉ ታደሰ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደተናገሩት የፍኖተ-ካርታው ራዕይ በከተማም ሆነ…


