የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የባህል እና ቱሪዝም ፅ/ቤት ፣ የድሬ ብድር እና ቁጠባ ተቋምን የግማሽ አመት የስራ አፈፃፀም ምልከታውን አድርጓል ።
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንደስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለ4ኛ ቀን የመስክ ምልከታውን ቀጥሎ ያካሄደ ሲሆን በዛሬው እለት የድሬደዋ አስተዳደር ባህል እና ቱሪዝም ፅ/ቤት እና በቱሪዝም ሚኒስቴር ቅንጅት እየተሰራ ያለ ላንድ ማርክ ፕሮጀክት አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ ምልከታ ካደረገ በኋላ ከዚራ የሚገኘውን የቅዱስ ሚናስ ቤተ ፀሎት፣ የአርመን ሀዋሪያዊት ቤተክርስቲያን እና ለገሀሬ ገንደ- ገበሬ የሚገኘውን…


