የሰብዓዊ እርዳታ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
አስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታ ለሚሹ ወገኖች ድጋፍ ለማዳረስ እየተሰራ መሆኑን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ፡፡ የአገልግሎቱ ሚኒስትር ዴዔታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ÷በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተከሰተውን የዝናብ እጥረት ተከትሎ በተለይም ከዚህ ቀደም በድርቁ ተጎጂ በነበሩ አካባቢዎች ያሉ ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ እንደሚሹ ተናግረዋል፡፡ ለእነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታ ለማዳረስም መንግስት ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡ በ2016…


