ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የፋሲል ግቢን መረቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል። የተከናወነው ሰፊ የእድሳት ሥራ በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን በማሻሻል አዲስ እስትንፋስ የሰጠ ሆኗል። የእድሳት ሥራው የቤተመንግሥቱን የግንባታ መዋቅር መጠገን፣ የእግር መንገዶችን ማሻሻል፣ ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ በባሕላዊ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ በማደስ…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር በዓለም ባንክ ድጋፍ የተተገበሩ ፕሮጀክቶች የነዋሪውን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸው ተመላከተ::

በዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ Urban Resilience and Land (URL), Practice Manager በሆኑት Mr. Abhas K. Jha የተመራ ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር በዓለም ባንክ ድጋፍ የተሰሩ ስራዎች ላይና ስራዎቹን አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ከአስተዳደሩ አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ፤ በመስክ በዓለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የተሰሩ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል። በዚህም በውይይት መድረኩ የተገኙት የፋይንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ወረዳ ሁለት አስተዳደር ጽ/ቤት በወረዳው የሚገኙ 410 የቀበሌ ቤቶችን ለድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ አስረከበ

የመንግስት ቤቶችን ምቹ በሆነ ሁኔታ ለማስተዳደር በተሻሻለው የአሰራር ስርአት መሰረት የቀበሌ ቤቶችን የአስተዳደር ሂደት ዲጂታላይዝ በሆነ መልኩ ለመምራትና ድሬዳዋ የምትገኝበትን የልማት ግስጋሴ በሚመጥን መልኩ የቀበሌ ቤቶችን ለመገንባት እና ለማዘመን ቤቶቹን በአንድ ማዕከል መሰብሰብ አስፈላጊ በመሆኑ ርክክብ መደረጉ ተመላክቷል። በዚህም በርክክብ መርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመንግስት ህንፃዎችና ቤቶች አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ኢብሳ…

Read More

አሽከርካሪዎች ስነምግባረን ተላብሰው በማሽከርከር እንዲሁም ህግና ስርአትን ተከትለው በመንቀሳቀስ ሊደርስ ከሚችል የመንገድ ላይ የትራፊክ አደጋ ራሳቸውን እና ማህበረሰባሀውን እንዲጠብቁ ጥሪ ቀረበ

የድሬደዋ አስተዳደር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ከድሬደዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ትራፊክ ዳይሬክቶሬት ጋር በመቀናጀት ለታክሲ ማህበራት ለባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በተለያዩ ርእሰጉዳዮች ላይ የሚሰጠው ስልጠና ዛሬም ቀጥሎ ተካሂዷል። መድረኩን በይፋ ያስጀመሩት በባስልጣኑ የህዝብ ጭነት ትራንስፖርት ስምሪት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈለቀ ፈረጃ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች በእለቱ መድረክ ሚተላለፉ መልክቶችን በአግባቡ በመውሰድ ወደ መሬት ሊያወርዱ እንደሚገባ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን የእለቱ መድረክም…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመስከረም እና ጥቅምት ወር 2018 ዓ.ም በመሠረተ ልማት፣ በገጠር ልማት፣ በአስተዳደራዊ ማሻሻያ እና በዲፕሎማሲያዊ ትብብር ላይ ያተኮሩ ተከታታይ አገራዊ እና ዓለም አቀፍ ተግባራትን አከናውነዋል። ያለፈውን ወር ተግበራት በጨረፍታ እነሆ፥

የከተማ ልማት እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በተመለከተ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ከዳንጎቴ ግሩፕ ጋር በመተባበር ለሚገነባው የዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካ እና በጎልደን ኮንኮርድ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ መሠረት መጣላቸው ከካናወኗቸው ቀዳሚ ተግባራት የሚጠቀሱ ናቸው። የጎዴ ነዳጅ ማጣሪያ ከሂላል የነዳጅ ስፍራ ድፍድፍ ነዳጅ በማውጣት፣ በማጣራትና በማጠራቀም በዓመት 3.5 ሚሊዮን ቶን…

Read More

ባለፉት 3 ወራት ብቻ በተመረቱ ተኪ ምርቶች ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማዳን ተችሏል – የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ነው ሲል የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። መንግሥት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለማምረት እንዲቻል የተኪ ምርት ስትራቴጂን በመቅረጽ ወደ ሥራ በመግባቱ ከፍተኛ ውጤቶች ተመዝገበዋል ብሏል አገልግሎቱ በመግለጫው። ስትራቴጂው የተረጋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲኖር፣ የወጪ-ገቢ ምርት እንዲመጣጠን እና ሀገራዊ ሉዓላዊነት እንዲረጋገጥ እያደረገ ይገኛልም ነው ያለው።…

Read More

በኢትዮጵያ ከ40 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ከተረጂነት ለማላቀቅ በአደጋ ስጋት መከላከል በኩል ተጨባጭ ውጤት ማስገኘቱ ተገለጸ።

“ከአደጋ ይልቅ ለአደጋ ስጋት አይበገሬነት ግንባታ ትኩረት እንስጥ” በሚል መሪ ቃል የአደጋ ስጋት ቅነሳ ቀን አከባበርን አስመልክቶ የተዘጋጀ መድረክ በድሬዳዋ ተካሂዷል። የአደጋ ስጋት ቅነሳ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ48ኛ ጊዜ፥በሀገራችን ደግሞ ለ16ኛ ጊዜ እንዲሁም በአስተዳደሩ ለ11ኛ ጊዜ ዘንድሮ እንደሚከበር ተገልጿል። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይ እና በከንቲባ ጽ/ቤት የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ዶ/ር…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን በባለፉት ሶስት ወራት ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ

በባለፉት ሶስት ወራት ከ1.7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን አስታውቋል። የትምህርትና ስልጠና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አክሊለ ታጠቅ በዛሬው እለት ለሚዲያ አካላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ባለስልጣን መስሪያቤቱ በባለፉት ሶስት ወራት 2.5 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 1.7 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብን እና በዚህም የእቅድን 85 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልጸዋል። አስተዳደሩ…

Read More

ኢትዮጵያ ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና የጀመረችውን ጉዞ ለማፋጠን የገጠሩን ኅብረተሰብ የአኗኗር ዘይቤ መለወጥ ወሳኝ ነው – አፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ትናንት ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝቱ የተሳተፉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሠ ጫፎ፥ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በተጀመረው ጉዞ ገጠሩን መቀየር ምን ዓይነት ለውጥ እያመጣ እንዳለ ተመልክተናል ብለዋል። አብዛኛው የሀገሪቱ ኅብረተሰብ የሚኖረው በገጠር ነው ያሉት አፈጉባዔ ታገሠ፤ ሀገሪቱ ወደ…

Read More

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቻፓ ኩባንያ ጋር በአጋርነት ለመሥራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከቻፓ ኩባንያ ጋር በአጋርነት መሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል ተፈራርሟል። የመግባቢያ ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገዱ ግሩፕ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኃይለመለኮት ማሞ እና የቻፓ ኩባንያ መሥራቾች ተፈራርመዋል። በስምምነቱ መሠረት ቻፓ ኩባንያ ደንበኞች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረ-ገፅ ላይ በሁሉም የክፍያ አማራጮች የቲኬት ግዢ አገልግልት እንዲያገኙ ያስችላል።…

Read More