የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት ልኡካን ቡድን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ድሬዳዋ አስተዳደር ገብተዋል
የልኡካን ቡድኑ አባላት ድሬዳዋ አስተዳደር ሲደርሱ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ባዩ እና የአስተዳደሩ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ልኡካን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚኖረው የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት በአስተዳደሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎች በመጎብኘት የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርግ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል ፡፡ በሱማሌ…


