የጥምቀት በአል በሰላም ይከበር ዘንድ አስፈላጊውን ሁሉ የቅድመ-ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸው ተገለፀ ።
በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የጥምቀት በአል ከነገ ጀምሮ ባሉት ቀጣይ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር በታላቅ ድምቀት የሚከበር ሲሆን ከዚሁ በአል ጋር ተያይዞ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ እስቂያስ ታፈሰ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል ። በአለም ቅርስነት የተመዘገበው የጥምቀት በአል ሲከበር የወንድማማችነትና የአብሮነት እሴቶቻችን ባጎላና ለአለም ህዝብ የጀመርነውን ኢትዮጲያዊ አንድነት ጎልቶ…


