በድሬዳዋ የጥምቀት እና ከተራ በዓል በደማቅ ሁኔታ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ መከበሩን ፖሊስ ገለፀ::

    የድሬደዋ ፖሊስ እንዳስታወቀው በሀይማኖታዊ ስርአቱ መሰረት ሁሉም ታቦታት በዝምሬና ምስጋና በሰላም ወደ የደብራቸው በሰላም መግባታቸውን ገልፆ ለበዓሉ ፍፁም ሰላማዊነት ምስጋናውን አቅርቧል:: ከጥምቀትና ከተራ በአል አከባበር ጋር ተያይዞ ለበአሉ ፍፁም ሰላማዊነት አስቀድሞ የበአል የፀጥታ እቅድ በማውጣት ወደ ስራ መግባቱን የገለፀው ፖሊስ በጥምቀት ሆነ ከተራ በአል ምንም አይነት የፀጥታ ችግርም ሆነ የወንጀል ተግባራት ሳይፈፀሙ እንዲሁም የትራፊክ አደጋ…

    Read More

      ለረጅም አመታት ኑሯቸውን በውጭ አገር ያደረጉ፤ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወንድምና እህቶች፤ ከናፈቁት የእናታቸው ማዕድ ለመቋደስ፤ የዘመናት እንባዋንም ለማበስ ወደ ትውልድ ከተማቸው ድሬዳዋ መግባት ቀጥለዋል።

      የእናታቸውን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር ቤት የገቡትና በድሬዳዋ ተወላጅ የሆኑት ወገን ወሰን፣ አደላሽ ክፍሌ፣ እና ስንታየሁ አርጋው፤ ዛሬ ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በከንቲባው ጽ/ቤት የዳያስፖራ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አቤል አሸብር እንግዶቹን በተቀበሉበት ስነ-ስርዓት ላይ፤ በድሬዳዋ የተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ ታዳጊ እግር ኳስ ቡድኖች ተጫዋችና አሰልጣኞቻቸው ተገኝተው፤ የእንኳን ደህና መጣችሁ…

      Read More

        መላው በድሬዳዋ አስተዳደር የምትገኙ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖት ተከታዮች በሙሉ፤ እንኳን ለ2014 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የፍቅር፣ የአንድነትና፣ የመረዳዳት በዓል ይሁንላችሁ።

        በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም፤ በሰው ልጅ ወካይ የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበውና ከሀገር መልካም ገፅታ ግንባታና፣ ከቱሪዝም እድገት አንፃር ጉልህ ሚና የሚጫወተው ኃይማኖታዊው የጥምቀት በዓል፤ በአገራችን ኢትዮጵያ ሉአላዊነት ላይ የተቃጣውን ጦርነት በህብረት መክተን፤ የልዩነት በሮችን በመዝጋት ለቀጣይ አገራዊ አንድነታችን ዝግጁ በሆንበት ወቅት የሚከበር ልዩ በዓል ነው። በአስተዳደራችን የምትገኙ የእምነቱ ተከታይ የሆናችሁ የበዓሉ ተሳታፊ ወገኖቼ…

        Read More

          የድሬዳዋ አስተዳደር ከዚህ ቀደም የምትታወቅበት የተለያዩ እምነት ተከታዮች በአላትን በጋራና በአንድነት የማክበር ባህል በጥምቀት በአል ላምይ በለገሀሬ ቀበሌ የቅዱስ ጊዮርጊስና የቅዱስ ኡራኤል ታቦት በሚያልፍበት ወቅት የእስልምና እምነት ተከታዮች ለክርስትና እምነት ተከታዮች የታሸጉ ውሀዎችን ከማቀበል ባለፈ የማስተባበር ስራዎችንም በመስራት ላይ ይገኛሉ ።

          Read More

            የመድኒያለም ታቦት በሰንበት ተማሪዎች በመዘምራን እና በምእመናን ዝማሬና ምስጋና ታጅቦ ከቅጥር ግቢው እየወጣ ነው። ቀፊራ ላይ አቡነ ከተክለሃይማኖት ታቦት ጋር በመገናኝት ወደ ጥምቀተ ባህር እያመሩ ነው።

            በአሉ እጅግ ሞቅ ደመቅ ባለ መልኩ እተከናወነ ሲሆን ቀፊራ ላይ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ለክርስቲያን ወንድሞቻቸው ውሃና ጣፋጭ ምግቦችን በማዘጋጀት በአሉን አብረው እያከበሩ ነው

            Read More

              ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ ወደ ከተማችን ድሬዳዋ የመጡ ዳያስፖራ ማህበረሰብ በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ በመገኘት ጉብኝት አደረጉ።

              ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያ ወደ ሀገር ቤት እንዲገቡ በተደረገው ጥሪ መሰረት የድሬዳዋ ዳያስፖራ ማህበረሰብ አስተዳደሩ ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በፕሮግራሙ መሰረት በድሬዳዋ ኢንዱስትሪ ፓርክ ወደ ውጭ መላክ የጀመሩ ፋብሪካዎችን የስራ እንቅስቃሴ የጎበኙ ሲሆን ለዳያስፓራ ማህበረሰብ በሚፈልጉበት ዘርፍ እንዲሰማሩና የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ ካሚል ኢብራሂም ጥሪ አቅርበዋል።

              Read More

                Content ¿cuáles Son Las Opiniones 1xbet Argentina? Bono Suprabets Retiro Antes De Que Finalice Su Juego Bet Argentina Y Reseñas Sobre Este Corredor De Apuestas Wager Perú: La Oferta De Apuestas Deportivas Las Mejores Casas De Apuestas Fuera De La Dgoj: Mercados E Cuotas 🏆 Android Paginas De Apuestas Deportivas Gratis Bono En Acumuladores De…

                Read More

                  ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት አባላት የጥምቀት በዓል የሚከበርበትን ስፍራ የፅዳትና የማስዋብ ስራ አከናውነዋል።

                  የድሬደዋ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የድሬዳዋ አገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ሃላፊ ሊቀ ብርሃናት ቀለመወርቅ ቢምረው ተግባሩ ወንድማማቻዊ አንድንትን በማጎልበት አብሮነትን በማጉላት የሃይማኖት መቻቻልን የሚያጠናክር ነው ብለዋል። ምእመኑ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በአሉን በፍፁም ሰላማዊ መንገድ እንዲከበር ማድረግ ይገባዋል ሲሉ ሊቀብርሃናት ቀለመወርቅ ቢምረው መልእክት አስተላልፈዋል። በሌላ በኩል የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ…

                  Read More