በድሬዳዋ አስተዳደር እሁድ ጠዋት ለትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዝግ እንዲሆን የተወሰነው ውሳኔ ላይ ማሻሻዮች ተደረገ ።

    በድሬዳዋ አስተዳደር በሳምንቱ መጨረሻ እሁድ ላይ ከጠዋት 12 ሰአት እስከ 4 ሰአት ድረስ በከተማዋ ላይ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ዝግ ከመደረጉ ጋር ተያይዞ ከዚህ ቀደም በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎች ሲነሱ ቆይተዋል ። በዚሁም ጉዳይ ዙሪያ ለመምክር በዛሬው እለት በራስ-ሆቴል መሰብሰብያ አዳራሽ ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት ተካሂዷል ። በተለይም እድሜያቸው የገፍ እናት አባቶች እንዲሁም የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እሁድ…

    Read More

      በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ ቀበሌዎች በተለያዩ ጊዜያት ሲከሰቱ የቆዩ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት ሁለቱ ክልሎች ከስምምነት መድረሳቸውን አስታውቀዋል። ገዳማይቱ ፣ እንዱፎ እና ገርበኢሴ በተባሉ አዋሳኝ ቀበሌዎች ይከሰቱ ነበሩ ግጭቶች ሞት እና መፈናቀል ከማስከተል ባለፈ ሁለቱን ክልሎች የቃል እሰጣ አገባ ውስጥ ሲያስገባቸው ቆይቷል። የአፋር ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ ጅግጅጋ ተገኝተው ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ እና ሌሎች ባለስልጣናት ጋር ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ማጠቃለያም ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ያስችላል የተባለ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

      Read More

        ዘንድሮ በድሬዳዋ ለሚኪያሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ቅድመ ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው::

        በድሬዳዋ አስተዳደር ዘንድሮ ለ4ተኛ ጊዜ ለሚኪያሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ አበረታች የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ የደን ልማት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ተናግረዋል። በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ከበደ ይማም የተመራ ቡድን ዛሬ ረፋድ ድሬዳዋ ተገኝቶ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ የተገነባውን ዘመናዊ የችግኝ ማፍያ ጣቢያና ለዘንድሮ አረንጓዴ አሻራ እየተካሄዱ የሚገኙትን እንቅስቃሴዎች ጎብኝቷል፡፡ በፌደራል መንግስት ድጋፍ በመላው አገሪቱ…

        Read More

          የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እያደረገ ባለው የመስክ ምልከታው የድሬዳዋ አስተዳደር የአነስተኛና መካከለኛ መኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ኮርፖሬሽንን የስራ አፈፃፀም ገምግሟል።

          ቋሚ ኮሚቴው በኮርፖሬሽኑ የተሰሩ በደበኛ ስራዎችን፣ ከዚህ በፊት በቋሚ ኮሚቴው የተሰጡ ግብረመልሶች እንዲሁም በህዝብ ውክልና የውይይት መደረኮች ኮርፖሬሽኑን በተመለከተ ከህዝብ የተነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ተቋሙ ያከናወናቸውን ተግባራት ገምግሟል። በዚሁ አግባብ ኮርፖሬሽኑ ያከናወናቸን ተግባራት በተመለከተ የአነስተኛና መካከለኛ መኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ክላስተር ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኡስማን አህመድ ለቋሚ ኮሚቴው ማብራሪያ ሰተዋል። አቶ ኡስማን በሰጡት…

          Read More

            በድሬዳዋ “ለፍቅር እሮጣለሁ” የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ነው በድሬደዋ በርካታ አላማዎች ያነገበ “ለፍቅር እሮጣለሁ” የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል።

            ውድድሩ የድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን በኮማንደር አትሌት ጌጤ ዋሚ ከሚመራው ሂማ ሬስ ኢንተርናሽናል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በሺዎች የሚገመቱ የድሬዳዋ ነዋሪዎች እና የአገራችን ታዋቂ አትሌቶች የተሳተፉበትን የ10ሺ እና የ5ሺ ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር፣ ታዋቂዋ አትሌት ኮማንደር ጌጤ ዋሚ፣ የአስተዳደሩ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ፊራንኦል ቡልቻ ሌሎች በርካታ እንግዶች ናቸው።…

            Read More

              የድሬ ዳዋ አስተዳደር ምክር ቤትን ካተማ ልማት፣ኮንስትራክሽንና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመስክ ምልከታ ዛሬ በ4ኛ ቀኑ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተመልክቷል ።

              የድሬ ዳዋ አስተዳደር ምክር ቤትን ካተማ ልማት፣ኮንስትራክሽንና ማዘጋጃቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመስክ ምልከታ ዛሬ በ4ኛ ቀኑ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተመልክቷል ። ኮሚቴው በዛሬው ዕለት በከተማው የተሰሩትና እየተሰሩ ያሉት በርካታ የልማት ፕሮጀክቶችን ሲጎበኝ የዋለ ሲሆን የኮንትራክሽንና ቤቶች ልማት ቢሮ ለቢሯቸው እያስገነባ ያለውን የ G+4 ና G+5 ህንፃ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ከባለፈው 3 ወር በፊቱ መልከታ ጋር በማነፃፀር…

              Read More