የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።
1ኛ :- የሴቶችን አኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቅረፍ በተለያዩ ገቢ ማስገኛ እንዲሰማሩ ለማስቻል በተቀረጸው ፕሮጀክት ዙሪያ ውይይት ተደርጎ አቅጣጫ የተሰጠበት ሲሆን 2ኛ:- የድሬዳዋ አስተዳደር የሰላም ምክር ቤት ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ውይይት ተደርጎ ደንቡ እንዲፀድቅ ውሳኔ ተላልፏል። 3ኛ:- በተጨማሪም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ካቢኔው በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል። የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ።


