በድሬዳዋ ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ
18ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በድሬዳዋ አስተዳደር በተለያዩ ሁነቶች በድምቀት ተከብሯል። “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጰያ ማንሰራራት የአዲስ ዘመን ድል ብስራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ’” በሚል መሪ ሀሳብ ነው የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከብሯሌ። ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት እመርታዊ ስኬቶችን ያስመዘገበችበት እና የማንሰራራት የከፍታ ዘመን የጀመረችበትን የድል ብስራት በሚያስቀጥሉ ሁነቶች ታጅቦ እየተከበረ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ በድሬዳዋ…


