“የ’World Without Hunger’ ጉባኤን ስናጠናቅቅ፣ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ውይይቶች የተሳኩ ይሆኑ ዘንድ አስተዋፅዖ ያበረከቱትን ተሳታፊዎች ከልብ አመሰግናለሁ።

አርባ ቢሊዮን ዛፎች በተተከሉበት ምርታማነትን በሚያሳድጉ የለውጥ ሥራዎች፣ ድርቅን በሚቋቋሙ አዝርዕት ልማት፣ በአረንጓዴዓሻራ መርሃ ግብር ሥራዎች አማካኝነት በዘላቂ የግብርና ሥራ የታየው የኢትዮጵያ ርምጃ በጉባኤው ቀርቧል። በ’ኢትዮዽያ ታምርት’፣ በአግሮ ኢንደስትሪ ፓርኮች ጥምር የሥራ ፈጠራ ሥራ፣ በገቢ እድገት እና ጽናት የታዩት ኢንቨስትመንቶች በአለም የግብርና ዘርፍ የኢትዮጵያን ሚና አጠናክረውታል። ረሃብን መዋጋት የጋራ ምላሽን ይሻል። ለዚህም ለምግብ ዋስትና የሚሆን…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና ውሀ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ለወረዳ እና ለቀበሌ አመራሮች ፣ ለግብርና ባለሞያዎች እንዲሁም ለአርሶ እና አርብቶ አደር ህብረተሰብ ተወካዮች በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍ የትውውቅና ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በአሁን ሰአት እየተካሄደ ይገኛል ።

ውድ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የፌስቡክ ገፅ ተከታታዮች በመድረኩ ላይ ያሉትን አጠቃላይ መረጃዎች ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል ። በአለማየሁ አበበ ፎቶ :- በሰላም አበበ +6

Read More

የድሬዳዋ “ደረቅ ወደብ በመልቲ ሞዳል አገልግሎት ባለፉት 3 ወራት 334 ኮንቴነር ማስተናገዱን እና በተያዘው ሩብ አመት 21 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለፁ ።

የድሬዳዋ “ደረቅ ወደብ ” በቀን ከ2400 በላይ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ያስተናግዳል :: ደረቅ ወደቡ በመልቲ ሞዳል አገልግሎት በያዝነው ሩብ አመት 334 ኮንቴነር ማስተናገድ መቻሉ ተገልጿል። በዚህም በሩብ አመቱ ከአገልግሎት 21 ሚሊየን ብር ትርፍ ማግኘቱን የድሬዳዋ ደረቅ ወደብ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል :: የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የድሬዳዋ ደረቅ ወደብ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም ታደለ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሴራሊዮን ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሴራሊዮን ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ማዳ ባዮን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋገረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጁሊየስ ማዳ ባዮን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን በማሕበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ፅሑፍ አስታውቀዋል።

Read More

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ለዶናልድ ትራምፕ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷በቀጣይ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር በጉጉባ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት 5 መቶ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የተማሪዎች ምገባ ፕሮጀክት ሊጀመር ነው

ኤልኔት ፋውንዴሽን ከድሬዳዋ ልማት ማህበር እና ከድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን 5 መቶ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግና በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኘው በጉጉባ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የሚተገበር የተማሪዎች ምገባ ፕሮጀክት ለማስጀመር የፊርማ ስነ-ስርአት በዛሬው ዕለት አካሄደ፡፡ በመርሀ ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አሊዪ እንደ ሀገር የደረሰብንን የትምህርት ስብራት ለመጠገን የምገባ ፕሮግራም ከፍተኛ…

Read More

“የ’World Without Hunger’ ጉባኤ ተሳታፊዎችን እንኳን ወደ አፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና በሰለም መጣችሁ እላለሁ።

አለምአቀፍ መሪዎችን፣ ባለሞያዎችን እና የጉዳዩ ተቆርቋሪዎችን በአንድ ላይ በማምጣት እንዲወያዩ በማድረግ የጋራ ጥረቶቻችን ረሃብን በማጥፋት ለሁሉም የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ርብርብ ፍሬ እንዲያፈራ እንደሚያስችሉ ተስፋ አለኝ። በኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ዓመታት በግብርና ሽግግር እና ምርታማነት ላይ በማተኮር የሠራነው ሥራ የታረሰ መሬታችን እጥፍ በማድረስ ከፍ ያለ እሴት ባላቸው የኢንደስትሪ አዝርዕት ምርት ላይ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች አስገኝቷል። በሚቀጥሉት ቀናት…

Read More

በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ የተመራ ልኡካን ቡድን ድሬዳዋ ከተማ ገባ

“ቁልፍ የመሰረተ-ልማት ደህንነት ለዲጂታል ሉአላዊነት” በሚል 5 ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ከጥቅምት አንድ ጀምሮ እየተከበረ ሲገኝ ይህንንም አስመልክቶ ሀገራዊ የሳይበር ደህንነት ፖሊሲ ትግበራ እና የባለድርሻ አካላት ሚና በሚል ርዕስ ከክልልና ከከተማ አስተዳደር አመራሮችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የተዘጋጀ የምክክር መድረክ ላይ ለመሳተፍ ነው ወ/ሮ ትዕግስት ወደ ድሬዳዋ የገቡት:: በዚህም ጥቅምት 25 እና 26/2017 አ.ም…

Read More

ከኢንዱስትሪው ዘርፍ የ12.8 በመቶ ዕድገት ይጠበቃል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በተያዘው በጀት ዓመት ከኢንዱስትሪው ዘርፍ የ12.8 በመቶ ዕድገት እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለፉት 3 ዓመታት በ”ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ የተሰሩ ሥራዎች ለዘርፉ መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል፡፡ ምርታማነትን ለማሳደግ በአምራች ዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመፍታት መንግሥት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በጨርቃ ጨርቅ፣ በምግብ እና መጠጥ፣ በኮንስትራክሽን፣ በኬሚካል እና በሌሎች…

Read More

በዓመት እስከ 130 ሚሊዮን ተጓዦችን የሚያስተናግድ ኤርፖርት እንገነባለን፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በአፍሪካ ግዙፍ የሚያስብለንን ትልቅ ኤርፖርት ለመገንባት ጥናት አጠናቀናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምክርቤት ማብራሪያቸው ወቅት ተናግረዋል። አሁን ያለው የቦሌ ዓለም ዓቀፍ ኤርፖርት በዓመት ከ25 ሚሊዬን ለማይበልጡ መንገደኞችን ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ በመሆኑ ይህን ለማሳደግ አዲስ ኤርፖርት መገንባት ማስፈለጉን ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል። በዚህም በዓመት ከ100 እስከ 130 ሚሊዮን ተጓዦችን ማስተናገድ የሚችል አዲስ ኤርፖርት ለመገንባት ጥናቱ…

Read More