ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመከላከያ ሠራዊት ጀነራል አመራሮች ጋር ተወያዩ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመከላከያ ሠራዊት ጀነራል አመራሮች ጋር በሀገራዊ እና ቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ “ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከመከላከያ ሠራዊታችን ጀነራል አመራሮች ጋር በሀገራዊ እና ቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል።” ብለዋል፡፡


