የድሬዳዋ ስታድየም አለም አቀፍ ጨዋታዎችን የማስተናገድ አቅሙን ለመገምገም የካፍ ከፍተኛ ባለሙያ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ላይሰንሲንግ ዳይሬክተር የተመራ ልዑክ ቡድን ጉብኝት አድርገዋል
የካፍ ልዑክ ቡድኑ በመጀመሪያ የድሬዳዋ ስታድየም አጠቃላይ ምልከታ ያደረጉ ሲሆን በተጨማሪም የድሬዳዋ ሆቴሎች እና ሆስፒታሎችን ተዟዙረው ተመልክቷል ። የድሬዳዋ ስታዲየም ገምጋሚ ልዑካን ቡድኑ በካፍ ኢንስፔክሽን ቢያንካ ብሬንዳ ሲመራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ላይሰንሲንግ ዳይሬክተር አቶ አመሀ ተስፋዬ ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን የድሬዳዋ ስታዲየምን የካፍን መስፈርት ለማሟላት…


