ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ሳልቫ ኬር ጋር ተወያዩ::

በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ በዛሬው ሁለተኛ ቀን ውሎው በተለያዩ ወሳኝ አህጉራዊ አጀንዳዎች ላይ ምክክሩን ቀጥሏል። በጉባኤው ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር ማያርዲት ጋር ተገናኝተው መክረዋል። መሪዎቹ በውይይታቸው በቀጣናዊ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ አተኩረዋል።

Read More

የድሬዳዋን የአብሮነትና መደጋገፍ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ::

የሆር ሙድ ጤና ቡድን 1447ኛው የረመዳን ፆም አስመልክቶ የተለያዩ የፍጆታ እቃዎች ድጋፍ አበርክቷል።በመረሀ ግብሩ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተጋባዥነት ተገኝተዋል። በድጋፉ መረሀ ግብሩ ተጋብዘው የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር እንደተናገሩት በአገር አቀፍ ደረጃ የማእድ ማጋራት የበጎ ፍቃድ ስራዎች በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተነሳሽነት መከናወን ከጀመረ ወዲህ በርካታ ተግባራት እየተፈፀሙ እንደሆነ ጠቁመዋል።…

Read More

ወርቃማ የወጣትነት ወቅት ላይ ትኩረቱን ያደረገው የወጣት ሙአዝ መሀመድ የነሺዳ አልበም ተመረቀ።

የወጣቶች ወርቃማ ጊዜያት ላይ ትኩረቱን ያደረገ አዲስ የነሺዳ ስብስቦችን የያዘ የወጣት ሙአዝ መሀመድ አልበም በርካታ የጥበብ አፍቃሪያን በገኙበት በዛሬው እለት በድምቀት ተመርቋል። በምረቃ መርሀግብሩም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ክብር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ተገኝተው እንደገለጹት ወጣቱ በነሺዳ አልበሙ በተለይም በለጋ እድሜው ለሀገር ለቤተሰብ የሚጠቅም ተግባራትን በጥበበ በማዋዛት ላበረከተው አስተዋጾ ምስጋና አቅርበዋል። ወጣቱ በርካታ ውጣውረዶችን በማለፍ ለዚህም…

Read More

የአዲስ አበባ ለውጥ ያስደነቃቸው አፍሪካውያን::

በመዲናዋ እየታየ ያለው ፈጣን የከተማ ልማት እና የውበት ለውጥ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ተሞክሮ እንደሚሆን በ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ የታደሙ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች ገለጹ። አዲስ አበባን ለመጀመሪያ ጊዜ ከስድስት ዓመታት በፊት ጎብኝተው እንደነበር ያስታወሱት ከኢስዋቲኒ የመጡት የጉባዔው ተሳታፊ ኪንታፒ ሮቢንስ፤ አሁን ያገኟት ከተማ ግን ፈጽሞ የተለየች መሆኗን ተናግረዋል። “አዲስ አበባ በየጊዜው እየተዋበች እና…

Read More

በድሬዳዋ የመጀመሪያ የሆነው የምሽት የጎዳና ላይ ሩጫ በድምቀት ተካሄደ::

ኑሩ ኢቨንት ከድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮምሽን እንዲሁም ከድሬዳዋ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን ጋር እና ከሌሎችም አጋር አካላት ጋር በጋራ በመሆን ” ለትንሿ ኢትዮጵያ እሮጣለው”በሚል መሪ ቃል ትላንት የምሽት የተዘጋጀው የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር አካሂዷል። በመርሃ-ግብሩ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና…

Read More

የኢትዮጵያ እና ጣሊያን ስትራቴጂካዊ ትሥሥር ለአፍሪካ-አውሮፓ ጠንካራ ግንኙነት

በጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ የሚመራው የጣሊያን መንግሥት “የማቴይ ዕቅድ” በሚባለው አዲስ የፖሊሲ ማዕቀፍ ከአፍሪካ ጋር ያለውን ግንኙነት በከፍተኛ ሁኔታ ቀይሮታል። ይህ ስትራቴጂ ጣሊያንን በአውሮፓ ኅብረት እና በአፍሪካ መካከል እንደ “ልዩ ድልድይ” የሚመድባት ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ደግሞ የአፍሪካ ኅብረት መመልከቻ እና የዲፕሎማሲ ማዕከል በመሆኗ ለዕቅዱ ስኬት እንደ ዋነኛ መልሕቅ ተመርጣለች። በኢትዮጵያ እና ጣሊያን መካከል ያለው ትሥሥር በእኩልነት…

Read More

የዓለም የፋይናንስ ሥርዓት ኢ-ፍትሐዊ መሆኑ የአፍሪካን የዕዳ ጫና አብዝቷል – አንቶኒዮ ጉቴሬዝ

የዓለም የፋይናንስ ሥርዓት ኢ-ፍትሐዊ መሆኑ አፍሪካ የዕዳ ጫና እንዲበዛባት ማድረጉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ተናገሩ። የአፍሪካን የዕዳ ጫና ለማቃለል የፋይናንስ ክፍፍሉ ለበለፀጉ ሀገራት ያደላበትን አሠራር መቀየር እና የልማት ባንኮች ብድር መጨመር አለባቸው ብለዋል ዋና ጸሐፊው። ለ39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ አዲስ አበባ የሚገኙት አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ በተለያዩ ወቅታዊ ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ ጋር ተወያዩ::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ ጋር በዘላቂ ልማትና በአፍሪካ የልማት ቅድሚያ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፤ “ከፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ ጋር መወያየት ሁልጊዜም አስደሳች ነው!” ያሉ ሲሆን፣ ውይይቱ ባለፈው ዓመት ከነበራቸው ቆይታ የቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል። በምክክራቸውም በዘላቂ ልማት፣ በኢኮኖሚ ዕድገት እና ለአፍሪካ ልማት መሰጠት በሚገባቸው የቅድሚያ ጉዳዮች ማተኮሩን…

Read More

የፋይዳ መታወቂያ እንደስሙ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ ምዝገባውን ያላከናወኑ የድሬዳዋ ነዋሪዎች ምዝገባ በማከናወን የመታወቂያው ባለቤት እንዲሆኑ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ም/ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ጥሪ አቀረቡ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ የፋይዳ መታወቂያ ባለቤት እንዲሆኑ በቅንጅትና በርብርብ እየተሰራ እንደሚገኝ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ገልፀዋል። በአስተዳደሩ በ2017 ዓ.ም በአጠቃላይ ከአምስት መቶ ሶስት ሺ (5 መቶ 3 ሺ) በላይ የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ መካሄዱን ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ጠቁመው በ2018 ደግሞ ከ 2 መቶ 30 ሺ በላይ ነዋሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን አብራርተዋል።…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እና የ 5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ አፈፃፀም ያለበት ደረጃ ተገመገመ::

በድሬዳዋ አስተዳደር የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ እንዲሁም ደግሞ የ 5 ሚሊዮን ኢትዮ ኮደርስ ምዝገባ እየተካሄደ ሲሆን እነዚህም ምዝገባዎች ያሉባቸው ደረጃ በዛሬው ተገምግሟል ። ከዲጂታል መታወቂያ ጋር ተያይዞ በድሬዳዋ አስተዳደር ያለው አፈፃፀም ጥሩ ቢሆንም ነገር ግን በቀጣይ 5 ወራት 133 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ማስመዝገብ እንደሚገባ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ…

Read More