“ለዜጎች ቀልጣፋ እና ውጤታማ አገልግሎት እየተሰጠ ነዉ… ” የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ
በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ እና ውጤታማ አገልግሎት መሰጠት መቻሉን የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀይር ሀጅኑር አስታወቁ። በአስተዳደሩ የመንግስት ተቋማትን በመጀመሪያ ምዕረራፍ ወደ ሪፎርም በማስገባት እና የአገልግሎት አሰጣጥን በማዘመን ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወኑን ገልጸዋል። ተቋሙ በመቶ ቀናት እቅድም የተቋማትን አገልግሎት ለማሻሻል የሰራተኛውን አቅም በማጎልበት እንዲሁም…


