ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የ110 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ::
ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለገጠር ፋይናንስና ልማት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል የ110 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ። ስምምነቱን የፈረሙት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሺዴ እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የፐብሊክ ዘርፍ ዳይሬክተር ሚስተር ዲደሪክ ዛምቦን ናቸው። የስምምነቱ ዋና ዓላማዎች በጥቃቅንና አነስተኛ የንግድ ዘርፎች ለተሰማሩ ዜጎች የፋይናንስ አቅርቦትን በማመቻቸት በመላ ኢትዮጵያ ዘላቂ የግብርና እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎችን ማሳደግ…


