ጊዜው የሚጠይቀውን አሰራር በመከተል ፈጣንና ጥራት ያላቸው መረጃዎችን በተለያዩ አማራጮች ለማህበረሰቡ የማድረስ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ
በድሬዳዋ አስተዳደር በ2016 ዓ.ም በኢንፎርሜሽን ኮምኒኬሽንና ሚዲያ ዘርፍ የተመዘገበውን ውጤታማ አፈፃፀም በ2017 በጀት ዓመት በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል ለኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ አካላት የእውቅናና የምስጋና መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት ተካሄደ:: በመርሀ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ በ2016 ዓ.ም በርብርብና በቅንጅት በመሆን በሚዲያና በኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተው፤ ለዚህም አስተዋፆ ላበረከቱ አካላት…


