የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የፀጥታ ሀይል ባካሄደው የጋራ ስምሪት እና በወሰደው ጠንካራ እርምጃ የሽብርተኛው የሸኔ ቡድን አባላትን በመደምሰስ እና በመማረክ ቡድኑ ይንቀሳቀስባቸው የነበሩ አካባቢዎችን ነፃ በማውጣት ወደ አስተማማኝ ሰላም መመለስ መቻሉ ተገለፀ።
በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ፤ የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የጸጥታ ሀይልን በመወከል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የፀጥታ ሀይል ባካሄደው የጋራ ስምሪት እና በወሰደው ጠንካራ እርምጃ 43 የጠላት ሀይል መደምሰሳቸውን የገለፁ ሲሆን “ጃል ሐረርጌ” የተሰኘው የቡድኑ መሪ ከተደመሰሱት መሀከል መኖሩን እና ጃል ቦባሳ የተሰኘ የቡድኑ ምክትል መሪ ደግሞ በውጊያ…


