በሀገር ጉዳይ ላይ አንድ አይነት አቋም በመያዝ በጋራ መሰለፍ እንደሚገባ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ የሆኑት አቶ ከድር ጁሀር አስታወቁ ።
የሰላም ሚኒስቴር ከድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህና ፀጥታ ጉዳዮች ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚገኙ 9 የከተማ እንዲሁም በ 38 ገጠር ቀበሌዎች ላይ በሚገኙ አካባቢዎች የሰላም ሚኒስቴር ባለሞያ በመመደብ ያለፍትን አራት ወራት ህብረተሰብ ተኮር የሆኑ ውይይቶች እንዲሁም የግለሰብ ችግር ፣ የአካባቢ ችግር ፣ የማህበረሰብ ችግር ፣ የአስተዳደር ችግርና የፌደራል ችግር በማለት ባሉት አጠቃላይ የፀጥታ ጉዳዮች ዙሪያ…


