በውጭና ሀገር ውስጥ የሚገኙ ቅን የድሬዳዋ ልጆችና ወዳጆች ተባብረው ለመልካ አቡነ አረጋዊ የሴቶች ገዳም መነኮሳት እና እህቶቻቸው ያደረጉት ድጋፍ የሰብዓዊነት ማሳያ በጎ ተግባር በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ገለጹ
በዛሬዉ ዕለት በዉጪ ሀገር የሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች መልካ በሚገኘዉ አቡነ አረጋዊ የሴቶች ገዳም በመገኘት የተለያዩ ድጋፎችን አበርክተዋል በድጋፍ አሰጣጥ ስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ለገዳሙ ለተደረገዉ ድጋፍ የተሰማቸዉን ልባዊ ደስታ የገለጹ ሲሆን ከተማችንን በማሳደግ ህብረተሰባችንን መለወጥ እንድንችል የመተባበር፣መደጋገፍ እና የመተጋገዝ ባህላችን በእጅጉ ማደግ አለበት ብለዋል ክቡር ከንቲባዉ ። በእለቱ ለገዳሙ የዳቦ…


