የድሬዳዋ አስተዳደር ለሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተሽከርካሪ ስጦታ አበረከተ::
የድሬዳዋ አስተዳደር ለአስተዳደሩ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ መገልገያ የሚሆን የመኪና ስጦታ አበርክቷል። በመርሀ-ግብሩም የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የመኪናውን ቁልፍ ለድሬዳዋ አስተዳደር ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ ሼህ ኢብራሂም ኢማም እንዲሁም ለድሬዳዋ አስተዳደር ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ሊቀብርሀናት ቀለመወርቅ ቢምረው አስረክበዋል:: ክቡር ከንቲባ ከድር የድሬዳዋ አስተዳደር የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ማህበረሰቡን በጎ ነገር በማስተማር…


