direcom

የአርጆ ዲዴሳ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት ለአገልግሎት ሲበቃ ግብርናውን የሚያሻግር ይሆናል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአርጆ ዲዴሳ የመስኖ ልማት ፕሮጀክትን የጎበኙ ሲሆን፤ የደረሰበት ደረጃም አስደናቂ መሆኑን መመልከታቸውን ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይኽ ትልቅ ፕሮጀክት በቅርብ ዓመታት ግንባታው ተፋጥኖ ወደ መጠናቀቂያው መቃረቡን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ ለአገልግሎት በሚበቃበት ጊዜም የተለያዩ የአዝርዕት ልማትን በመደገፍ እንደሀገር የተጀመሩ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረቶችን የሚያግዝና በሺዎች የሚቆጠሩ አርሶ አደሮችን በመጥቀም ግብርናውን የሚያሻግር እንደሚሆን ገልጸዋል። ይኽ…

Read More

ኢትዮጵያን በሐሳብና በዕውቀት የመምራት ውጤቱ በልማት ሥራዎች እየተንፀባረቀ ነው – አቶ ተመስገን ጥሩነህ

የለውጡ መንግሥት ወደ ሥራ ከገባ በኋላ የተመዘገቡ ስኬቶች ሀገርን በሐሳብና በእውቀት የመምራት ውጤቶች መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገልጹ። የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ በተመረቀበት ወቅት አቶ ተመስገን በአደረጉት ንግግር፤ ቀደም ሲል በሀገሪቱ የነበረው ትልቁ ፈተና የሐሳብና የራዕይ ማነስ እንደነበር አስታውሰዋል። እነዚህን ክፍተቶች በመሙላትና ለተግባራዊነቱም ሌት ከቀን በመሥራት፣ አሁን ላይ ኢትዮጵያ በግልጽ የሚታይ የዕድገትና…

Read More

ከትላንት ቁጭት እስከ ዛሬው የልማት ፀሐይ፤ የወለጋ አዲስ ገጽታ

ተፈጥሮ ሳትሰስት ጸጋዋን የቸረችው፣ ለም መሬትና ማዕድናት የሞሉበት፣ ምቹ አየር የታደለው የወለጋ ምድር፤ ለዘመናት የጸጋውና የገጽታው መራራቅ የሕዝቡ የቁጭት ምንጭ ሆኖ ቆይቷል። የአካባቢው ሕዝብ አጠገቡ እያየውና እየዳሰሰው በቁጭት የሚንገበገብለት የተፈጥሮ ሀብት ለምቶ ኑሮው እንዲሻሻል የዘመናት ምኞቱ ነበር። ይህን የሕዝብ መሻት የተረዱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሰባት ዓመታት በፊት በነቀምት ከተማ ተገኝተው ከሕዝቡ ጋር በነበራቸው…

Read More

አዲስ የተገነባው የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ እውነታዎች

• በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዕድገት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ ምዕራፍ የሚጠቀሠው የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ ከውጭ የሚገባውን የድንጋይ ከሰል ፍላጎት ለመተካት የሚያግዝ ነው። • የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር በሚገኘው ብሔራዊ ማዕድን ኮርፖሬሽን የሚተዳደር ነው። • ፋብሪካው ለኢትዮጵያ ዕድገት ወሳኝ ለሆኑት የሲሚንቶ፣ የብረት ብረት እና የማምረቻ ኢንዱስትሪዎች የድንጋይ ከሰል ያቀርባል። • ፋብሪካው በሰዓት…

Read More

የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ሽግግር ያፋጥናል – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ

የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ በይፋ መመረቁ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያስፈነጥር መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋብሪካውን መመረቅ አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ፋብሪካው በተለይም ከውጭ የሚገባውን ምርት በመተካት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንደሚኖረው አመልክተዋል። ከዚህም ባለፈ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር እና የሀገር ውስጥ ፋብሪካዎች ለኃይል አቅርቦት የሚያወጡትን የማጓጓዣ ወጪ…

Read More

የተጀመረውን ልማት እና ብልፅግና ለማስቀጠል ሰላምን ማጽናት ያስፈልጋል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የተጀመረውን ልማት እና ብልፅግና ለማስቀጠል ሰላምን ማጽናት ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቄለም ወለጋ ዞን የቄጦ የመስኖ መሠረተ ልማት ፕሮጀክትን በጎበኙበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኦሮሞ ሕዝብ ሰላም ወዳድ መሆኑን ለማሳየት ልጆቹን ነጋሳ እና ነጋሶ በማለት ይሰይማል ብለዋል። ሕዝቡ ሰላም ዋነኛ እሴቱ እና መለያው እንደሆነ ገልጸው፤ ልዩነትን በውይይት እንደሚፈታ ለማሳየት ልጆቹን…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

የአርጆ የድንጋይ ከሰል ፋብሪካ፤ ከውጭ ሲገባ የነበረውን የተፈጨ ድንጋይ ከሰል ፍላጎት በሀገር ውስጥ በማሟላት በኢትዮጵያ የዘርፉ የኢንደስትሪ ልማት ዐቢይ ሚና ይጫወታል። ፋብሪካው ለሲሚንቶ፣ ለብረት እና ኮንስትራክሽን ኢንደስትሪዎች አስፈላጊ ጥሬ ግብዓቶችን ያቀርባል። በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃን በማረጋገጥ የኢንደስትሪ ልማትን እንደምታሳድግ ማሳያ ነው።

Read More

የተፈጥሮ ኃብትን በኃላፊነት የማልማት አይነተኛ ማሳያ የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምዕራብ ወለጋ ዞን ገንጂ ወረዳ የሚገኘውን የቱሉ ካፒ የወርቅ ልማት ፕሮጀክትን ጉኝተዋል። በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ፕሮጀክቱ የተፈጥሮ ኃብታችንን ለሀገርና ለሕዝብ ጥቅም በኃላፊነት እንዴት ማዋል እንደምንችል የሚያሳይ አይነተኛ ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል። በመንግሥት እና በግል ኢንቨስተሮች ትብብር እየተከናወነ የሚገኘው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት፣ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ባሻገር የአካባቢውን ማኅበረሰብ የኑሮ ደረጃ የሚያሻሽሉ በርካታ…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የጎበኙት የሃዋ ገላን አርሶ አደሮች ጽናትና የሙዝ እርሻ ስኬት::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቄለም ወለጋ ዞን ሃዋ ገላን ወረዳ ተገኝተው በ”ሌማት ትሩፋት” መርሃ-ግብር የለማ የሙዝ እርሻን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል። አርሶ አደሮቹ መሬትና የውኃ ኃብትን በአግባቡ በመጠቀም፣ ባህላዊ የመስኖ ዘዴዎችን በማቀናጀት አካባቢያቸውን ወደ ተስፋ ሰጪ የግብርና ማዕከልነት መለወጣቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ተመልክተዋል። በተለይም የመንገድ መሠረተ ልማት መገንባት የአርሶ አደሩን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ ለማድረስ…

Read More

የቄጦ የመስኖ ፕሮጀክት፤ ለሰዲ ጫንቃ እና ሃዋ ገላን ወረዳዎች አዲስ የልማት ተስፋ::

ለሰዲ ጫንቃ እና ሃዋ ገላን ወረዳዎች ትርጉም ያለው ለውጥ እያመጣ የሚገኘው የቄጦ የመስኖ መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ለግብርናው ዘርፍ አዲስ ገጽታ እየፈጠረ ይገኛል። ፕሮጀክቱ የአካባቢውን የተፈጥሮ መልክዓ-ምድር በአግባቡ በመጠቀም፣ ለግብርና ሥራ የማይቋረጥ የውኃ አቅርቦት እንዲኖር ታስቦ የተተገበረ ነው። በአሁኑ ወቅትም የመስኖ ሥራውን በቀጥታ ጥቅም ላይ በማዋል የታረሰ እና የለማ መሬት ለኅብረተሰቡ ጉልህ ፋይዳ ማስገኘት ጀምሯል። ከመስኖው…

Read More