#ዜና | በድሬዳዋ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።

የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አቡበከር አዶሽ በዛሬው ዕለት የ201 7 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በትምህርት ቤቶች ቅኝት በማድረግ ጭምር በይፋ ያስጀመሩ ሲሆን በቢሯቸውም መግለጫ ሠጥተዋል። አቶ አቡበከር የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መከፈት አስመልክቶ በሠጡት መግለጫ በተቀመጠው መስፈርት መሠረት ምዝገባዎች በአብዛኛው በመጠናቀቃቸው የ2017 ዓ.ም ትምህርት ዛሬ መስከረም 7 በይፋ መጀመሩን ገልጸዉ በትምህርት ሴክተር የተሰማሩ…

Read More

#ዜና የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለ2017 የትምህርት ዘመን ለአቅመ ደካማ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ለትምህርት ቢሮ አስረክቧል

አንድም ሕፃን በመማሪያ ቁሳቁስ አጥረት ምክንያት ከትምህርት መቅረት የለበትም በሚል መርህ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ያበረከተ ሲሆን፤ ድጋፉንም ለድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስረክቧል፡፡

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር ሀገራዊ የምክክር መድረክ በዛሬው ውሎ ባለድርሻ አካላት በቡድን ያደራጁትን የተጠቃለለ አጃንዳቸውን አቅርበዋል ።

በድሬዳዋ አስተዳደር በሀገራዊ የምክክር መድረክ እየተሳተፉ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በዛሬው የአምስተኛ ቀን ውሎ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የማህበራትና ተቋማት፣ የመንግስት አስፈጻሚ አካላትና የታዋቂ ግለሰቦች ወኪሎች ተወያይተው የተስማሙባቸውን አጀንዳዎች በመረጧቸው የቡድን መሪዎች አማካኝነት ለጋራ መድረኩ አቅርበዋል:: ከባለድርሻ አካላት የተመረጡ ወኪሎች ከአምስቱ ባለድርሻ አካላት የተሰበሰቡ የድሬዳዋ አስተዳደር አጀንዳዎችን አደራጅተውና አጠናቅረው በጋራ መድረኩ ካቀረቡ በኋላ በቀጣይ ጊዜያት…

Read More

“የክልሉ የጸጥታ ኃይል ከፌዴራል የጸጥታ ኃይል ጋር በመኾን አካባቢውን ለመጠበቅ እና ወታደራዊ እርምጃ ለመውሰድ በቂ ዝግጅት አለው” የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ባሕር ዳር: ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኀላፊ እሸቱ የሱፍ (ዶ.ር) በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫቸውም ክልሉ አንድ ዓመት በሞላው የሰላም እጦት ውስጥ መቆየቱን አንስተዋል፡፡ ከሐምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ክልሉ እስካሁን ድረስ የሰላም መደፍረስ ችግር አጋጥሞት መቆየቱን ነው የተናገሩት፡፡ የክልሉን የጸጥታ ሁኔታ ለመቀየር መንግሥት በርካታ የሰላም አማራጮችን ማቅረቡን የተናገሩት ምክትል ኀላፊው ሰላማዊ ውይይቶች ሲተገብር መቆየቱን ነው የተናገሩት፡፡ ጥያቄ እና ሃሳብ አለኝ የሚል እንዲቀርብ እና ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ጥረት መደረጉንም አስታውሰዋል፡፡…

Read More

ሁለንተናዊ የልማት ሥራዎቻችን “ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና” በሚል የጀመርነውን ራዕያችንን በሚያሳካ መንገድ እየተተገበሩ ነው፡- ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ.

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በድሬዳዋ የተመለከቷቸው የሥርዓተ ምግብ፣ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድን፣ የልማት ትሩፋት እና የነፃ የንግድ ቀጣና ሥራዎች የተሳሰረ የልማት ፓኬጅ ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል። በጉብኝታቸው በሥርዓተ ምግብ መርሐ ግብር ተጠቃሚ የሆኑ ነዋሪዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ በምግብ ራሳቸውን መቻላቸውን እንዲሁም ልጆቻቸውም የተመጣጠነ ምግብ እያገኙ እንደሆነ ማየታቸውንም አመልክተዋል። በማኅበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሥርዓት የተጀመሩ ሥራዎችም…

Read More

ወጣቶች በተስፋ የተሞሉ የለውጥ ሀይል ሊሆኑ እንደሚገባ ተገለፀ::

የአሰሊሶ ወረዳ ከድሬደዋ ወጣቶችና ስፓርት ኮምሽን ጋር በመተባበር በወረዳው ለሚገኙ 500 ወጣቶች የማነቃቂያና የህይወት ተሞክሮ ስልጠና ሰጥቷል። የአሰሊሶ ወረዳ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዲ አበደላ ወጣቶች በአንድ አገር አጠቃላይ እድገትና መፃዒ የለውጥ ስኬት ትልቁን ድርሻ የሚወስዱ አምራች ሃይል እንደሆኑ አውስተዋል።በአስተዳደራችን ወጣቱን በሙሉ ሃይል በማህበራዊ ፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መድክ ተሳታፊ ከመሆን ባለፈ ለሚኖረው ለውጥ ባለቤት እንዲሆኑ የሚያስችሉ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በአስተዳደሩ የሚከናወኑ ትልልቅ ሁነቶችን በቀጥታ ስርጭት ሽፋን መረጃዎችን በሶስቱም ቋንቋዎች የማሰራጨት ስራን መስራቱ የመረጃ ተደራሽነቱ እንዲስፋፋ ማስቻሉ ተገለፀ

የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የ2016 ዓ.ም የስራ አፈፃፀም እና የልካም አስተዳደር ሪፖርት ግምገማ መድረክ እንዲሁም የ2017 ዓ.ም ዕቅድ ላይ የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡ በውይይት መድረኩ የ2016 በጀት አመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2017 ዓ.ም እቅድ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር ሪፖርት የተቋሙ ሰራተኞችን ጨምሮ የሴክተር ተቋማትና የወረዳዎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በመድረኩ…

Read More

“በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ዓሻራችንን እናኑር”፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነሐሴ 17 ቀን 2016 ዓ.ም በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ዓሻራችንን እናኑር ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። በአንድ መንፈስ በመላው ኢትዮጵያ ዓሻራችንን እናኑር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንድ ከሆን ከዚህም በላይ እንችላለን! ሲሉ ገልፀዋል። አዋቂዎች ከ20 በላይ፣ ታዳጊዎች ከ10 በላይ ችግኞችን በመትከል ለሀገር ያለንን ፍቅር፣ ለትውልድ ያለንን ስጦታ በተገቢው ስፍራ እንግለጥ ሲሉ…

Read More