የካቢኔ ውሳኔዋች

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ዛሬ ከሰአት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዋች ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል። 1ኛ:- የከተማ ወረዳዎች አደረጃጀት ላይ ተወያይቶ አፅድቋል። 2ኛ:- የከተማ መሬት ይዞታ አገልግሎቶች ተመን ማሻሻያ ላይ ካቢኔው ተወያይቷል። 3ኛ:- የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት ማቋቋሚያ ደንብ ካቢኔው ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል። በመጨረሻ ካቢኔው በመሬት እና መሬት ነክ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን አስተላልፏል። የድሬዳዋ…

Read More

የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ ፀደቀ

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ከተለያዩ ሹመቶች በተጨማሪ 3 ረቂቅ አዋጆችን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነምግባር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፉ የልማት ማህበር መካከል የዘላቂ እና ንፁህ ኢነርጂ ተደራሽነት ለማፋጠን ፕሮግራም ማስፈፀሚያ…

Read More

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የፓን አፍሪካ እሳቤ አዲስ አብነት ነው፡- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ታላቁ የኢትዮጵያ ግድብ ከኃይል ማመንጫ ግድብነት ባሻገር በራስ አቅም የራስን መሻት ማሳካት እንደሚቻል ያሳየ የፓን አፍሪካ እሳቤ አዲስ አብነት መሆኑን የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ተናገሩ። የሩስያው አርቲ ሚዲያ ባዘጋጀው የአፍሪካ ሚዲያ እውቅና መድረክ የሚታደሙ የሀገራት የኮሙኒኬሽን እና ኢንፎርሜሽን ሚኒስቴሮች እና ተወካዮች፣ የቀድሞ የፓን አፍሪካ መሪዎች ልጆች፣ የአፍሪካ ሀገራት የሚዲያ ተቋማት ኃላፊዎች…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር ከ 2 ሺ 4 መቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክትን ወደ ስራ ለማስገባት ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደረገ::

ኤስ ኦ ኤስ (SOS) የህፃናት መንደር በድሬዳዋ አስተዳደር ለ አምስት ዓመታት የሚተገበር ”Green growth -empowering youth for green future project ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ሲሆን በዛሬው ዕለት ፕሮጀክቱን ወደ ስራ ለማስገባት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ…

Read More

“ኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ በየክልሎች የሚከናወኑ ከ17 ዓመት በታች የስፖርት እንቅስቃሴዎችን በከፍተኛ ደረጃ ያነቃቃል።”:-የድሬዳዋ እግር ኳስ ፌዴሬሽን

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ እና የድሬዳዋ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪካ ዋንጫ በማለፉ የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ለመላዊ ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ብሄራዊ ቡድኑ ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት ተሰቶ በመሰራቱ የተገኘ ድል መሆኑን ኮሚሽነር አለሙ ገልፀው፤ የኢትዮጵያ ከ17…

Read More

በ10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም የድሬዳዋ አስተዳደር አፈጻጸም ሪፖርት ተገመገመ

10ኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም በሰመራ ሎጊያ ከተማ ከህዳር 6 እስከ 10 መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ወደ ስፍራው ያቀናው የአስተዳደሩ ልዑክ ቡድን የተሳትፎ የአፈጻጸም ሪፖርት በአስተባባሪ ኮሚቴ ቀርቦ ተገምግሟል። በመድረኩም የድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ልማት ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ጀማል ኢብራሂም አስተዳደሩ በዘንድሮ የከተሞች ፎረም ከዚህ ቀደም ከነበረው ተሳትፎ የተሻለ ስራዎች ይዞ መቅረቡን ጠቅሰው በ14 ዘርፍ እና…

Read More

ለኤች አይ ቪ ተጋላጭነትን በመቀነስና ከሙስና የፀዳ ትውልድ በመፍጠር ጠንካራ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር መፍጠር ይገባል ተባለ

የዘንድሮው የአለም የፀረ ሙስና ቀን “ትውልድን በስነ ምግባር ፤ ተቋምን በአሰራር! ” በሚል መሪ ቃል ለ22ተኛ ጊዜ እየተከበረ ሲሆን የአለም የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን ደግሞ ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽን ዘላቂነት ማረጋገጥ በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ38 ኛ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ37 ኛ ጊዜ በአስተዳደራችን ድሬዳዋ በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ…

Read More

ወጣቶች ሁሌም በበጎ ፍቃድ ስራዎች በመሰማራት አካባቢያቸውን የመንከባከብና ማህበረሰባቸውን የመጥቀም ስራ መስራት እንደሚገባቸው ተገለፀ

የብልጽግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የወጣቶች ክንፍ የ2018 ዓ.ም የበጋ ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስመልክቶ የፅዳት ዘመቻና የችግኝ እንክብካቤ አከናውነዋል። በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ይሱፍ ከወጣቶች ጋር በመተባበር የፅዳት ዘመቻ መከናወኑን እንዲሁም በ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራ መሰራቱን ገልፀዋል። በተለይም ወጣቶች ሁሌም በበጎ…

Read More

ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ አዲስ ቅርንጫፉን በሃረማያ አስመረቀ

ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ተደራሽነቱን በማስፋት በማያ ሲቲ በሃረማያ ከተማ አዲስ ቅርንጫፉን በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ የፋይናንስ ተደራሽነቱንና አካታችነቱን በማጠናከር የተቋሙ ታላሚ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም መጠነኛ ገቢ ያላቸውና አነስተኛ ገቢ በሚያስገኙ ሥራዎች የተሰማሩትን ብሎም ወጣቶችና ሴቶችን በስፋት በሚሰጣቸው የብድርና ቁጠባ አገልግሎቶቹ እየደረሰ ይገኛል። ዛሬም የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት አዲስ ቅርንጫፉን በታሪካዊው የሃረማያ ሃይቅ…

Read More

የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭትን ለመግታት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተገለፀ::

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት አመራር እና ሰራተኞች ዛሬ ከሰዓት በኋላ የኤች አይ ቪ ኤድስ እና የነጭ ሪቫን ቀንን አከበሩ። “ተግዳሮቶችን በመቋቋም የኤች አይ ቪ ኤድስ ምላሽን ማረጋገጥ ” በሚል መሪ ቃል በኢትዮጵያ ለ 37ኛ ጊዜ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ38ኛ ጊዜ የሚከበረው አለም ዓቀፍ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀንን እና “ጥቃትን የማይታገስ ማህበረሰብ…

Read More