በዘንድሮ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ 11 ሺ አባወራዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቧል::
በድሬዳዋ አስተዳደር በአሰሊሶ ክላስተር ለገዶን ገጠር ቀበሌ “የአፈር ሀብታችን ለብልፅግናችን” በሚል የ2017 ዓ.ም የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ መክፈቻ መርሀ ግብር ተካሄደ። በመርሀ ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽፈት ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻኪር አህመድ ባለፉት አመታት በህዝብ ንቅናቄ በተሰሩ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ከ50 ሺ ሄክታር በላይ መሬትን ማልማት እንደተቻለ፤ እንዲሁም የአፈር ለምነትን…


