የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ፣ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት የ2017 ዓ.ም 2ተኛ ሩብ አመት ማጠቃለያ ኮንፍረንስ ዛሬ ተካሄደ።
”ከቃል ወደ ባህል” በሚል መሪ የተካሄደው መድረክ በቢሮውና ተጠሪ ተቋማት የብልፅግና ፓርቲ አባላት የተገኙበት መድረክ ተካሂዷል ። በመድረኩ ላይ የተገኙት የቢሮው ምክትል ኃላፊና አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ዳይሬክተር አቶ አብዲ ሙክታር እንደገለፁት ባለፉት ስድስት ወራት በመሠረታዊ ድርጅት የታቀዱ እቅዶችን ከግብ ለማድረስ በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ ገልፀዋል። በተለይም አዳዲስ አባላትን ከማፍራት አንፃርና በሰው ተኮር ስራዎች ላይ…


