የአስተዳደራችን ነዋሪዎች በክረምት በጎ ፍቃድ የጤና ምርመራና የህክምና አገልግሎት ዘመቻን በመጠቀም ያለምንም ክፍያ የጤና ምርመራ ማድረግ እንደሚገባቸው ተጠቆመ፡፡
‹‹በጎነት ለጤናችን›› የሚል መሪ ሃሳብ ያለው የነፃ የጤና ምርመራና ህክምና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘመቻ በዛሬው ዕለት የአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃርና የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ተጠሪ አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም እንዲሁም ሌሎች የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡ በመክፈቻ መረሃ-ግብሩ ተገኝተው የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ነፃ የጤና ምርመራና ህክምና ዘመቻውን በይፋ ያስጀመሩት የአስተዳደሩ…


