የናሽናል ሲሚንቶ አክስዮን ማህበር የማህበረሰብ አቀፍ ተግባራትን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።
የናሽናል ሲሚንቶ አክስዮን ማህበር በድሬዳዋ አስተዳደር በከተማም ሆነ በገጠር በተለያዩ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት ስራዎች ላይ በስፋት በመሰማራት ዘርፈ-ብዙ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ። ፋብሪካው በድሬዳዋ አስተዳደር ለረጅም ጊዜያት በመብራት እጦት ሲቸገሩ ለነበሩ የኢጃነኒ የገጠር ቀበሌ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደረገና በ 5 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ወጪ የትራንስፎርመር ተከላና የመስመር ዝርጋታ ሙሉ ወጪ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት ችሏል። ከዚህ…


