የብልፅግና ፓርቲ 5ተኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክቶ ከህዳር 2 እስከ ህዳር 6 የሚቆይ የፎቶ አውደ-ርዕይ በድሬዳዋ አስተዳደር ተጀመረ።

#DGC | ህዳር 2/2017 ዓ.ም በዛሬው ዕለት በተለምዶ ኮንጎ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ በሚገኘው የወጣቶች ማዕከል አዳራሽ የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን አስመልክቶ በአስተዳደሩ ባሉ የሴክተር ተቋማትና ወረዳዎች የተከናወኑ ስራዎችን የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ-ርዕይ ተጀመረ። በፎቶ አውደ ርዕዩ ላይ በእንግድነት ተገኝተው በይፋ ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር እንደተናገሩት ብልፅግና ፓርቲ ከህዝብና ባለድርሻ አካላት ጋር…

Read More

የደቡብ ሱዳን የግብርና እና የምግብ ዋስትና ሚኒስቴር ሚኒስትር ፣ የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራምን የሚደግፍ ከልማት ተቋማት የመጡ የኔዘርላንድ ምክትል አምባሳደር ፣ የአይሪሼድ የፕሮግራምን የሚደግፍ አጋር ድርጅት እና ፕሮግራም ሀላፊዎች ፣ የብሪቲሽ ኤምባሲ ፕሮግራም ሀላፊ ፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር ፣ ከግብርና ሚኒስቴር እንዲሁም ከማህበራዊ ጉዳይ የመጡ ባለሞያዎች በዛሬው እለት ድሬዳዋ ገብተዋል ።

ድሬዳዋ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ፣ የድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና ውሀ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ኑረዲን አብደላ እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደር የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ከድር አሊይ ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Read More

ድሬ ቪአይፒ ጤና ቡድን በአጠቃላይ ውጤት 8 – 2 አሸናፊ ሆነ ።

ድሬ ቪአይፒ ጤና ቡድን ከ ድሬ ጤና ቡድን በዛሬው እለት የእግር ኳስ ጨዋታቸውን በድሬዳዋ ኢንተርናሽናል ስታዲየም ያካሄዱ ሲሆን የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር ለድሬ ቪአይፒ ጤና ቡድን ፣ አክሊል በድሩ እና ቢኒያም ይትባረክ ለድሬ ጤና ቡድን ባስቆጠሯቸው ጎሎች 2 ለ 2 በሆነ ውጤት ጨዋታው አልቋል ። ከዚህ ቀደም ድሬ ቪአይፒ ጤና ቡድን ከ…

Read More

የህልም ጉልበት፤ ለእምርታዊ እድገት” በሚል መሪ ቃል 4ኛ ዙር የብልፅግና ፓርቲ አባል ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ስልጠና መሰጠት ጀመረ።

#DGC | ጥቅምት 29 / 2017 ዓ.ም በዚህም በዛሬው እለት በጠዋቱ መርሀ-ግብር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮና የኮንስትራክሽን ቢሮ ፣ የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ፣ የከንቲባ ፅ/ቤትና ተጠሪ ተቋማት፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤትና ተጠሪ ተቋማት፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ እንዲሁም ፐብሊክ ሰርቪስና የድሬዳዋ አስተዳደር ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ ስልጠናውን መስጠት የጀመሩ ተቋማት ናቸው። ስልጠናው የፓርቲ አባላቶችን…

Read More

የብልፅግና ፓርቲ 4ኛው ዙር “የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት” ስልጠና ለከንቲባ ፅ/ቤትና ለተለያዩ ተቋማት ለመሠረታዊ ድርጅት ኣባላት ስልጠና መስጠት ተጀመረ ።

#DGC ጥቅምት 29/2017 በአስተዳደሩ ለከንቲባ ጽ/ቤትና በስሩ ለሚገኙ ተቋማት አባላት በተዘጋጀው ስልጠና ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደርጉት የከንቲባና የካቢኔ ጉዳዮች ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ብልፅግና ፓርቲ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ አካታች፣አሳታፊና ሁሉንም ዓይነት ኢትዮጵያዊ ብዝሃነትን ይዞ የተፈጠረ አገራዊ ህብረ-ብሔራዊ ፓርቲም ነው ብለዋል። ከተመሠረተ ገና አጭር ጊዜ ቢሆንም መጠነ ሰፊ የሪፎርም ሂደት ውስጥ የሚገኝና ዓይነተ ብዙ ዕመርታ…

Read More

“የህልም ጉልበት ለእምርታዊ እድገት ” በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ አባል ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች 4 ተኛ ዙር ስልጠና በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ ።

በዛሬው እለት ማለትም ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም የተጀመረውና የብልፅግና ፓርቲ አባል ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች የሚሰጠው ስልጠና በዋናነት የብልፅግና ፓርቲ አባላትን የግንዛቤ አድማስ የሚያሰፋ ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ የልማት ስራዎች እና ለሀገራዊ ሁለንተናዊ ብልፅግና ስኬት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲወጡ የሚያግዝ ነው ። ከዚህ በተጨማሪም የብልፅግና ፓርቲ ያለፉት አምስት ዓመታት በተለይም በፖለቲካ ፣ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተሰሩ በርካታ…

Read More

Rakkoolee Hanqina Dhiyeessa Bishaan Dhugaatii hir’isuuf tumsi hawaasa hundaa murteessaadha jedhan.

Itti Aanaan Kantiibaa Bulchiinsa Dirree Dhawaa Obbo Harbii Buuh waltajjii marii Abbaan Taayitaa Bishaanii fi dhangala’aa Bulchiinsaa Gaggeesota Gurmaa’iinsa Bilookii Aanaa 03, 04, 05 fi 06 waliin sababoota Hanqina Dhiyeessa Bishaan Dhugaatii Dirree Dhawaa fi Rakkoolee kana hir’isuuf hawaasni faalamaa fi Qisaasama bishaan Dhugaatii haala irrisuuf shoora gumaachuu qaban irratti marii gaggeefame irratti Rakkoolee Hanqina…

Read More

ሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን መከላከል የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ

#DGC ጥቅምት 28/2017 የድሬዳዋ አስተዳደር የስነ-ምግባር እና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ከተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ የመንግስት ተቋማት ሰራተኞች ሙስና ወንጀሎችን መከላከል ፤ በስነ-ምግባራዊ አመራር እና በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጠ። የድሬዳዋ አስተዳደር የስነ-ምግባር እና የጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ፌኑስ አብዱጀባር በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ሙስና የአንድን ሀገር ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገትን በመግታት ረገድ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር…

Read More

“የ’World Without Hunger’ ጉባኤን ስናጠናቅቅ፣ እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ውይይቶች የተሳኩ ይሆኑ ዘንድ አስተዋፅዖ ያበረከቱትን ተሳታፊዎች ከልብ አመሰግናለሁ።

አርባ ቢሊዮን ዛፎች በተተከሉበት ምርታማነትን በሚያሳድጉ የለውጥ ሥራዎች፣ ድርቅን በሚቋቋሙ አዝርዕት ልማት፣ በአረንጓዴዓሻራ መርሃ ግብር ሥራዎች አማካኝነት በዘላቂ የግብርና ሥራ የታየው የኢትዮጵያ ርምጃ በጉባኤው ቀርቧል። በ’ኢትዮዽያ ታምርት’፣ በአግሮ ኢንደስትሪ ፓርኮች ጥምር የሥራ ፈጠራ ሥራ፣ በገቢ እድገት እና ጽናት የታዩት ኢንቨስትመንቶች በአለም የግብርና ዘርፍ የኢትዮጵያን ሚና አጠናክረውታል። ረሃብን መዋጋት የጋራ ምላሽን ይሻል። ለዚህም ለምግብ ዋስትና የሚሆን…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የግብርና ውሀ ማእድንና ኢነርጂ ቢሮ ለወረዳ እና ለቀበሌ አመራሮች ፣ ለግብርና ባለሞያዎች እንዲሁም ለአርሶ እና አርብቶ አደር ህብረተሰብ ተወካዮች በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍ የትውውቅና ማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በአሁን ሰአት እየተካሄደ ይገኛል ።

ውድ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የፌስቡክ ገፅ ተከታታዮች በመድረኩ ላይ ያሉትን አጠቃላይ መረጃዎች ወደ እናንተ የምናደርስ ይሆናል ። በአለማየሁ አበበ ፎቶ :- በሰላም አበበ +6

Read More