“የወረዳ 07 የኮሪደር ልማት ለአካባቢው ንግድ እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው” – በወረዳ 07 የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ።
በድሬዳዋ ወረዳ 07 እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ለአካባቢው ንግድ እንቅስቃሴ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን በወረዳው የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብና ነዋሪዎች ገለፁ። ከኮሪደር ልማቱ በፊት አካባቢው ባረጁ ቤቶች፣ በሸራና በማዳበሪያ የተሞላ እንደነበረ የጠቀሱት አስተያየት ሰጪዎቹ በአሁኑ ሰዓት በኮሪደር ልማቱ የንግድ ሱቆችን በአዲስና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የመገንባት ስራ በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝና ይህም ለአካባቢው…


