የአፋን ኦሮሞ ቋንቋን ተረትና ምሳሌ የያዘው “ማክማክሳ” መፅሀፍ ተመረቀ

3 ሺ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋን ተረትና ምሳሌ የያዘው “ማክማክሳ” የተሰኘ መፅሀፍ በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቋል። በመድረኩ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የብልፅግና ፓርቲ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በምርቃት ስነ-ስርአቱ ላይ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው፤ መፅሀፉ ለተማሪዎች እንዲሁም ለመላው ማህበረሰብ እንደሚጠቅም ገልፀዋል። አቶ ኢብራሂም አያይዘውም እንደነዚህ አይነት ባህልና ወግን ለትውልድ የማስተላለፍ ስራ ላይ በመሰማራታቸው…

Read More

የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በድሬዳዋ አስተዳደር ባሉ አብያተ ቤተክርስትያናት በልዩ ሁኔታ ተከበረ

የስቅለት በዓል ድሬዳዋ በመንበረ ደብረ ሰላም መድኃኒዓለም ካቴድራል ሲከበር የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር በቤተክርስትያኑ በመገኘት ጣፉጭ ምግቦችን ፣ዳቦ እና ውሀ በማቅረብ የስቅለት በአልን አክብረው ለሚወጡ ምዕመናን ብርታትና ጥንካሬን ተመኝተዋል። በተመሳሳይ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ምክትል ከንቲባ. እና የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ፣የብልፅግና ፖርታ ድሬዳዋ…

Read More

የጸሎተ ሐሙስ ( ህጽበተ ሐሙስ) ስነ-ስርዓት በድሬዳዋ ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ተካሒዷል፡፡

ክርስቶስ የደቀመዝሙራቱን እግር ዝቅ ብሎ ያጠበበትን የትህትና ምሳሌ የጸሎተ ሐሙስ ( ህጽበተ ሐሙስ) ስነ-ስርዓት የድሬዳዋ ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሊቀ ብርሃናት ቀለመወርቅ ቢምረው የካህናቱንና የምእመናኑን እግር በማጠብ ፈጽመዋል ፡፡ የድሬዳዋ ወረዳ ሶስት የእስልምና እምነት ተከታይ ወንድሞችና እህቶች የጸሎት ስነ-ስርዓቱን ፈጽመው ለሚወጡ ምእመናን ውሃ ዳቦና ንፍሮ አዘጋጀተው በመጠበቅ ያላቸውን ፍቅርና…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የወረዳ 3 የእስልምና እምነት ተከታይ የሆኑ እህት ወንድሞች በቅድስት ማሪያም ካቴደራል ቤተክርስትያን በመገኘት የፀሎተ ሀሙስን ስነ-ስርአት አከናውነው ለወጡ የእምነቱ ተከታዮች የታሸጉ ውሀዎችን እና ድፎዳቦ የመስጠት መርሀ-ግብር በዛሬው እለት አካሄዱ ።

በመርሀ ግብሩ ላይ ያነጋገርናቸው የእስልምና እምነት ተከታይ እህት ወንድሞች የዛሬው ፕሮግራሞችን እንደሁሌውም ፍቅራችንን እና አብሮነታችንን ለማሳየት ያዘጋጀነው ነው በማለት ተናግረዋል። አስተባባሪዎቹ አያይዘውም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

Read More

ፀሎተ ሀሙስ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ ተከበረ

መላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በፆም፣ በፀሎትና በስግደት የሚከበረው ፀሎተ ሀሙስ በዛሬው ዕለትም በድሬዳዋ ቅድስት ማሪያም ካቴደራል ቤተክርስትያን በተለያዩ ስነ-ስርአቶች ተከብሯል ። በዚህም ክርስቶስ ዝቅ ብሎ የሀዋርያቱን እግር በማጠብ ትህትናውን የገለፀበትን ተግባር በማሰብ “ህጽበተ እግር” ተከናውኗል። በፀሎተ ሀሙስ እየሱስ ክርስቶስ ታላቅ መንፈሳዊ ሚስጥርን የገለጠበት በፀሎት መትጋትንና ትህትናን በተግባር ያስተማረበት እንደሆነም ቀሲስ ደበበ ተመስገን ተናግራዋል። በአሉን…

Read More

በድሬዳዋ በበጋ ወራት የበጎ ፍቃድ ስራ የተገነቡ ቤቶች ለአቅመ ደካሞች ተላለፉ

በአስተዳደራችን የበጋ ወራት የበጎፈቃድ መርሃ ግብር የአቅመ ደካማ መኖሪያ ቤቶች የመልሶ ግንባታ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የበጋ ወራት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ስራ ላይ ህብረተሰቡን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸው ተገልጿል፡፡ በድሬደዋ አስተዳደር በበጋ ወራት የበጎ ፍቃድ የልማት ተግባራት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የተለያዩ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽነር አቶ…

Read More

ህዝቡን እየጎዳ የሚገኘውን የኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር በመንግሥት እና በፓርቲ በኩል ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው – አቶ አደም ፋራህ

ህዝቡን እየጎዳ የሚገኘውን የኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር በመንግሥት እና በፓርቲ በኩል ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ ገለፁ። የብልጽግና ፓርቲ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል። መድረኩ ሶስተኛ ቀኑን የያዘ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት፣ ከስራ ዕድል ፈጠራ እና የተረጂነት አመለካከትና…

Read More

በኤችአይቪ/ኤድስ ላይ የሚታየው ቸልተኝነት ይቁም….

ወጣቶችን ጨምሮ ለበሽታው ተጋላጭ ተብለው በተለዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ላይ እየታየ ያለው የኤች አይቪ/ኤድስ የሥርጭት ምጣኔ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ እየተነገረ ይገኛል፡፡ በዘንድሮው የአለም ኤድስ ቀን “የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤችአይቪ መከላከል” በሚል መሪ ቃል ህዳር 2016 ዓ.ም ታስቦ መዋሉ ይታወቃል፡፡ ማህበረሰቡ ኤች.አይ.ቪን በመከላከል ረገድ የሚጫወተው የማይተካ ሚና በአገር አቀፍ ደረጃና እስከታች ባለው የመንግስት መዋቅርና በማህበረሰብ አደረጃጀት…

Read More

የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች አባላት ልኡካን ቡድን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ድሬዳዋ አስተዳደር ገብተዋል

የልኡካን ቡድኑ አባላት ድሬዳዋ አስተዳደር ሲደርሱ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማርቆስ ባዩ እና የአስተዳደሩ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ የሱማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች ልኡካን በድሬዳዋ አስተዳደር በሚኖረው የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት በአስተዳደሩ የተከናወኑ የልማት ስራዎች በመጎብኘት የልምድ ልውውጥ እንደሚያደርግ የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል ፡፡ በሱማሌ…

Read More