በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማውን ገጽታ ማራኪ ከማድረግ ባሻገር ለወጣቱ ሰፊ የስራ እድል የፈጠሩ መሆናቸው ተገለፀ።

በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 4 እና 5 እየተከናወኑ የሚገኙ የኮሪደር ልማት ስራዎች ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድልን ፈጥረዋል። በዚህም በወረዳዎቹ እየተሰሩ በሚገኙ የኮሪደር ልማት የስራዎች የስራ እድል ተፈጥሮላቸው ሲሰሩ ያነጋገርናቸው ወጣቶች የኮሪደር ልማቱ በሰፊው የስራ እድልን እንደፈጠረላቸው ገልፀዋል። ስራውን በጥራትና በፍጥነት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅም በርብርብና በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ወጣቶቹ አመላክተዋል። የኮሪደር ልማት ስራው ከጊዜ ጋር ሊሄዱ…

Read More

በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሀገሪቱ የኃይል ትሥሥር መቶ በመቶ እንዲረጋገጥ ይሰራል፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት በመላው ኢትዮጵያ ያለው የኃይል ትሥሥር መቶ በመቶ እንዲረጋገጥ ይሰራል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ትልም እውን እንዲሆን እና ዕድገት እንዲረጋገጥ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ማዳረስ ወሳኝ ነው፡፡ የዲጂታል 2030 መጀመር ይፋ በሆነበት መድረክ ላይ በተካሄደው ውይይት፤ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት ሳይሟላ የሚረጋገጥ እድገት እንደማይኖር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)…

Read More

ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የሚረዳ መሠረተ ልማትን ማስፋፋት እና ለዚሁ ሥራ የሚያግዝ የኃይል ትስስርን መፍጠር ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን የዘርፉ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ ይገልጻሉ።

በተጠናቀቀው የ”ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025″ ስትራቴጂም ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ ድርሻ ያላቸው የተለያዩ የቴሌኮም ዘርፍ ሥራዎች ተከናውነዋል። በዚህም አጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 97 ሚሊዮን ሲደርስ፤ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር ደግሞ ወደ 57 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ ይፋ በተደረገበት ወቅት ገልጸዋል። በመላ ሀገሪቱ በተደረገው መጠነ-ሰፊ የማስፋፊያ ሥራም…

Read More

የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በየዘርፉ መጠቀም እንደ አገር ያለውን እድገት ለማፋጠን እንደሚረዳ ተገለፀ።

በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የተማራ ልዑክ በኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጄንስ ኢኒስቲትዩት ጉብኝት አድረጓል። በጉብኝቱ ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር በድሬደዋ አስተዳደር ዘመናዊ አስተዳደርን በመዘርጋት ስማርት ሲቲን ለመፍጠር የሚያስችሉ ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው ለአብነትም የመሶብ አንድ ማእከል አገልግሎት እንዲሁም በፍትህ ዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን ጠቅሰዋል። ዝርዝሩን ይጠብቁን

Read More

“በኮሪደር ልማቱ አካባቢያችንን ለማሳመር የጀመርነውን ስራ አጠናክረን እናስቀጥላለን”:- የድሬዳዋ ነዋሪዎች

በኮሪደር ልማቱ አካባቢያችንን ለማሳመር የጀመርነውን ስራ አጠናክረን እናስቀጥላለን ሲሉ በድሬዳዋ የወረዳ 4 እና 5 ነዋሪዎች ተናገሩ። በድሬዳዋ አስተዳደር ዘጠኙንም የከተማ ወረዳዎች በኮሪደር ልማት አካባቢዎችን ውብ፣ ማራኪና ለነዋሪዎች ምቹ የማድረግ ስራ እየተከናወነ ሲገኝ፤ የወረዳ 4 እና 5 የኮሪደር የልማት ስራም የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን የማስዋብ፣ በመንገድ ከፈታ የተሽከርካሪና የእግረኛና መንገዶችን የማስፋት፣ የመንገድ ዳር መብራትና ሌሎችንም መሰረተ ልማቶችን ባካተተ…

Read More

“በከፍተኛ ርብርብ የጠላት ፍላጎትን ከንቱ በማድረግ የአስተዳደሩን ሰላም ያስጠበቁ ጀግኖችን ማመስገን ይገባል”። :- የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር

የድሬዳዋ አስተዳደር ሰላምን በላቀ ጀግንነትና የአመራር ጥበብ በማስጠበቅ ብሎም ግዳጆችና ተልዕኮችን በብቃት ለመሩና ለፈፀሙ ጀግኖች፣ ተቋማትና ደጋፊ አካላት የዕውቅናና የምስጋና መርሃ-ግብር ማምሻውን አካሂዷል። በቅርቡ የኦነግ ሸኔ የሽብር ቡድን ድሬዳዋን ጨምሮ በምስራቅ አጎራባች ክልሎች የሽብር ስራዎችን በመስራት ሰላምና ፀጥታን ለማደፍረስ ሲንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን፤ ድሬዳዋን ጨምሮ የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የጸጥታ ኃይል በጀግንነት በሽብር ቡድኑ ላይ በወሰደው ጠንካራ…

Read More

በድሬዳዋ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ስራን በማስፋፋት እና በማሳመር ድጋፍ እያደረግን ነው… የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች

በድሬዳዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን አዲስ ገጽታ በመቀየር ለነዎሪዎቿ ምቹ እንድትሆን ማስቻሉን ያየንበት እና የተጀመረው የኮሪደር ልማት ስራን በማስፋፋት እና በማሳመር ድጋፍ እያደረግን ነው ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ። እየተሰሩ ያሉት የኮሪደር ልማት ስራዎች የከተማዋ ዳግም ውልደት የፈጠሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል። የኮሪደር ልማት ነዋሪዎችን ተጠቃሚ በማድረጉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንደሚወጡም ገልጸዋል። የድሬዳዋ የወጣቶች እና ስፖርት…

Read More

የካቢኔ ውሳኔዎች

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ከአስተዳደሩ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቷል በዚህም:- 1ኛ:- ከዚራን በኮሪደር ልማት መልሶ የማልማት ሂደት ላይ ውይይት አድርጓል። 2ኛ:-የተሻሻለው የቦታ መነሻ ዋጋ ላይም እንዲሁ ካቢኔው ተወያይቷል። በተጨማሪም ካቢኔው በሌሎች የልማት እና የልማት ነክ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ተኛ የስራ ዘመን 5ተኛ አመት 3ተኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄዷል::

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ተኛ የስራ ዘመን 5ተኛ አመት 3ተኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሄዷል የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ተኛ የስራ ዘመን 5ተኛ አመት 3ተኛ አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳዎች አፅድቋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት 3ተኛ የስራ ዘመን 4ተኛ አመት 10ተኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ አፅድቋል እንዲሁም የተለያዩ ሹመቶችን ያፀደቀ ሲሆን በዚህ መሰረት:- 1,የአስተዳደሩ ምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ…

Read More