በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የተመራ የአመራሮች ልዑካን ቡድን በሀረር ከተማ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት::

የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በማስመልከት የገፅታ ግንባታና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ለማጠናከር በሀረሪ ክልል እና በድሬዳዋ አስተዳደር በጋራ የተዘጋጀ የምርጫ ቅስቀሳና የወዳጅነት መርሃ-ግብር በሀረር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በመርሃ-ግብሩ የሚኖሩ ሁነቶችን እየተከታተለ የሚያደርሳችሁ ይሆናል!!

Read More

ታሪካዊው የቀፊራ የንግድ ማዕከል በዘመናዊ መልክ ታድሶ በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል።

ታሪካዊው የቀፊራ የገበያ ሥፍራ በኮሪደር ልማት እድሳት እና ተጨማሪ የማሻሻያ ሥራዎች ተከናውኖለት በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል። በዚህም በምርቃት መርሃ ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር የቀፊራ መታደስ ለከተማዋ የንግድ እንቅስቃሴ አዲስ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል። ከንቲባ ከድር አያይዘውም ይህ ፕሮጀክት የታሪክና የዘመናዊነት ውህደት የታየበት መሆኑን ገልፀው፤ የቀፊራን ነባር ማንነት ሳይቀይር ለነጋዴዎች ምቹና ከጸሐይና…

Read More

በመጋቢት እና ሚያዝያ 2018 ዓ.ም ወራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሳይንሳዊ የምርምር ልህቀት፣ በከተማ ልማት፣ በኢኮኖሚ ሪፎርም እና በቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ዙሪያ ያተኮሩ የተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ክንውኖችን አድርገዋል።

‎ ‎• የፕሮጀክቶች ምረቃ እና የሥራ ጅማሮ ‎የመጋቢት ወር በተለያዩ ዘርፎች በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የተመረቁበት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ውስጥ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል መርቀዋል። ይህ ማዕከል 40 የላብራቶሪ ክፍሎችን እና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራት የሚያረጋግጥ የባዮ-ኢኩቫለንስ (bioequivalence) ማዕከልን ያካተተ ነው። ‎ ‎በከተማ ልማት ዘርፍ፣ የሚያዝያ ወር በአገልግሎት እና በዲጂታል መሠረተ-ልማት…

Read More

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን “ጎበዝ ሶላር ሴል” ማምረቻን ጎበኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ በሁዋጂያን ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ የሚገኘውን “ጎበዝ ሶላር ሴል” ማምረቻን ጎብኝተዋል። ‎ይህ ፋብሪካ በ2025 ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም (Invest in Ethiopia Forum) አማካኝነት በተፈረመው ስምምነት መነሻ በ100 ሚሊዮን ዶላር የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ የተቋቋመ ነው። ‎ ‎በውጤታማ ድጋፍ እና ክትትል በስድስት ወራት ብቻ እውን የሆነው “ጎበዝ…

Read More

የስንዴ ነዶን መምረጥ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት አጠናክሮ ማስቀጠል መሆኑ ተገለፀ::

በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር በሴቶች አስተባባሪነት የተዘጋጀ የብልፅግና ፓርቲ የአደባባይ የምርጫ ቅስቀሳ በድምቀት ተካሂዷል። በዚህም በቅስቀሳው ላይ የተገኙ ተሳታፊዎች ፓርቲው ባለፉት ዓመታት የሴቶችን ሁለንተናዊ ኑሮ ለማሻሻል የወሰዳቸው እርምጃዎች አበረታች መሆናቸውን ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪዎቹ አያይዘውም ብልፅግና ፓርቲ የሴቶችን የኑሮ ጫና የሚቀንሱ የልማት ሥራዎችን በተግባር በማሳየቱ የተጀመረው የለውጥ ጉዞ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አመላክተዋል። በአስተዳደሩ የተገነቡ የተለያዩ ማህበራዊ…

Read More

ሰራተኛው ከመቼውም ጊዜ በላይ በከፍተኛ የሥራ ስነ-ምግባር፣ በታማኝነትና በቅንነት ህዝቡንና ሀገሩን እያገለገለ እንደሚገኝ ገለፁ

ዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን (ሜይ ዴይ) በዛሬው እለት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በታሪክ ሰራተኞች ለመብታቸው የታገሉበት ነው። ዕለቱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ሞተር የሆነው ሰራተኛ ለሀገሩ እያበረከተ ያለውን የማይተካ ሚና የሚዘከርበትና የሚከበርበት ልዩ ቀን ነው። በዚህ በዓል ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ የድሬዳዋ ነዋሪዎች በአሁኑ ወቅት ሰራተኛው ከመቼውም ጊዜ በላይ በከፍተኛ የሥራ ስነ-ምግባርና በታማኝነት…

Read More

የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በሁሉም ዘርፎች እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ

በድሬዳዋ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ሴቶች ክንፍ አባላት “ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል የፊታችን ግንቦት ወር የሚካሄደውን 7ኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫን ምክንያት በማድረግ የብልፅግና ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ በእግር ጉዞ ጨምሮ በተለያዩ መርሃ-ግብሮች አከናውነዋል። በመርሃ-ግብሩ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር እንደገለጹት፣ ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሴቶች በፓርቲው ውስጥ በአመራርነትና በአባላትነት ያላቸው…

Read More

በሁሉም ዘርፍ የሚገኙ የሀገራችን ሰራተኞች

ከመቼውም ጊዜ በላይ በከፍተኛ የሥራ ስነ-ምግባርና በታማኝነት ህዝቡንና ሀገሩን እያገለገለ እንደሚገኝ ተገለፀ:: ዓለም አቀፍ የላብ አደሮች ቀን (ሜይ ዴይ) በታሪክ ሰራተኞች ለመብታቸው የታገሉበት ነው። ዕለቱ የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ሞተር የሆነው ሰራተኛ ለሀገሩ እያበረከተ ያለውን የማይተካ ሚና የሚዘከርበትና የሚከበርበት ልዩ ቀን ነው። በዚህ በዓል ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ የድሬዳዋ ነዋሪዎች በአሁኑ ወቅት ሰራተኛው…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የትንሳኤ በዓል እየሱስ ክርስቶስ በደሙ የሰው ልጆችን ከሀጢአት ለማንጻት ራሱን አሳልፎ በመሰጠት ወደር የማይገኝለት ፍቅሩን በመስቀል ላይ ገልፆ በሞቱ ለሰዉ ልጆች ሁሉ ምህረት ያስገኘበት እና ሞትንም ድል በመንሳት ከሞት የተነሳበት በዓል መሆኑን ኃላፊው በመልዕክታቸው ገልፀዋል። ትንሳኤ የተስፋ፣ የእምነት እና የአዲስ ህይወት ጅማሮ ምልክት እንደመሆኑ ይህ በዓል በልባችን ሰላምን፣ በማህበረሰባችን አንድነትን፣ በሀገራችንም ብልጽግናና እድገትን ይዞ ይመጣ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የትንሳኤ በአልን አስመልከቶ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ::

በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የአንድነት እንዲሆን የተመኙት ክቡር ም/ከንቲባው ፤ ያለንን በማካፈል፣ ጐረቤትን በማገዝ እና በመጠየቅ እንዲሁም የተቸገሩትን በመርዳት በአሉን በጋራ ማሳለፍ እንደሚገባ በመልዕክታቸው ገልፀዋል። በዓሉ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የመቻቻል እሴቶች ይበልጥ የሚጠናከሩበት ሊሆን እንደሚገባ ክቡር ም/ ከንቲባው ጠቁመው፤ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የፍቅር፣ የሰላም፣ የደስታ፣ የብልፅግና እና የመተሳሰብ በአል ይሆን ዘንድ መልካም…

Read More