ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት በመከተል ፍላጎታችንን ለማሳካት እየሰራን ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የምግብ ሥርዓት በመከተል የወደፊት ፍላጎታችንን ለማሳካት እየሰራን ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በ2ኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ስትራቴጂና ፖሊሲዎችን ቀርፃ ተግባራዊ እያደረገች ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከመጀመሪያው የተመድ የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በኋላ፣ ከሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር…

Read More

ዓለም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በአንድነት የሚቆምበት ጊዜው አሁን ነው፦ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ

ዓለም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በአንድነት የሚቆምበት ጊዜው አሁን ነው ሲሉ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ገለፁ። ፕሬዚዳንቱ ይህን ያሉት በአዲስ አበባ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በመካሄድ ላይ ባለው 2ኛው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ ነው። በዓለም አቀፍ ደረጃ የምግብ ሥርዓታችን አሁን ከመቼውም በላይ በፈተና ውስጥ ያለ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ አካታች የሆነ የምግብ ሥርዓት ለማረጋገጥ በትብብር መስራት አስፈላጊ…

Read More

ኢትዮጵያ በመደመር ያሳካችውን ለጉባኤው ለማጋራት ዝግጁ ነች፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ስታስተናግድ እንደ መሰብሰቢያ ብቻ ሳይሆን ሁሉን አካታች በሆነው መደመር ያሳካቻቸውን ግቦች እና ዓላማዋን ለማጋራት ዝግጁ መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለሁለተኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ተሳታፊዎች በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የእራት ግብዣ አድርገዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእራት ግብዣው ላይ ባደረጉት ንግግር፥ “የተሰባሰብነው ራት…

Read More

የናፍቆት ድሬ መርሀ ግብር በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ብሔር ብሔረሰቦችን የሚያቆራኝ እና አብሮነትን የሚያሳይ መሆኑን የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ተናገሩ።

የናፍቆት ድሬ ሳምንት በዘንድሮው ዓመት ለአራተኛ ጊዜ መከበር ጀምሯል ። በመጀመሪያ ቀን መርሀግብር “የናፍቆት በድሬ ፌስቲቫል” በነምበርዋን ኮሪደር ልማት ላይ በአስተዳደሩ የሚኖሩ የብሄር ብሄረሰቦች የባህል እና የወግ እቃዎች ትዕይንት እና የጣፋጭ ምግቦች ቅምሻ ተካሂዷል። ፌስቲቫሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ተገኝተው አስጀምረውታል። ለተሳታፊዎች ስለመርሀግብሩ ገለፃ እየሰጡ እና ከጣፋጭ ምግቦቹ እያስቀመሱ ባማረ ሁኔታ ተካሂዷል።…

Read More

ሀገራት ለብዝኀ ሕይወት እና ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት በመስጠት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ አለባቸው፡- አንቶኒዮ ጉተሬዝ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በ2ኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባዔ በበይነ መረብ ለታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕለክት፤ ሀገራት ለብዝኀ ሕይወት እና ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት በመስጠት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ አለባቸው ብለዋል። ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ከተመድ ጋር በመተባበር 2ኛውን የምግብ ሥርዓት ጉባኤ በጋራ በማዘጋጀታቸው ዋና ጸሐፊው አመስግነዋል፡፡ ሀገራት በመደበኛ በጀታቸው ውስጥ ለአካባቢ ጥበቃ እና የብዝኀ ሕይወት…

Read More

የምግብ ዋስትና ችግር ዓለምን ወደ ከፋ ቀውስ የሚመራ ትልቅ ፈተና ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ

አካባቢን በማልማት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ አለመቻል ተስፋ መቁረጥን በመፍጠር ወደ ግጭት፣ ሽብርተኝነት እና ፍልሰት የሚያመራ የዓለም ስጋት መሆኑን የጣሊያን ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሚኒስትሮች ምክርቤት ፕሬዚዳንት ጆርጂያ ሜሎኒ ገለጹ። በአዲስ አበባ እየተካሄደ ባለው ሁለተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባዔ ላይ ላይ ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሯ፥ ጉባኤው በአፍሪካ ሲካሄድ የመጀመሪያው መሆኑን ጠቅሰው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ…

Read More

በ4 ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት “ዓለማቀፍ የድሬዳዋ ቀን’ በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ዛሬ ማለዳ ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ከምድር ባቡር አደባባይ መነሻውን ያደረገ ስፖርታዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ተከትሎ የእግር ጉዞ በአስተዳደሩ የተከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች ጉብኝት እንደዚሁም ባለፉት ሶስት ዓመታት የናፍቆት ድሬ ሳምንታት የነበሩ የበዓሉን አጠቃላይ ገፅታ የሚያስቃኝ የፎቶ አውደ ርዕይ እና የድሬ ጣፋጭና ባህላዊ ምግቦች ቅምሻ መርሐግብሮች ተከብሯል ። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ የተከበሩ አቶ ከር ጁሀርና…

Read More

በ4ተኛው ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት “አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን” በተለያዩ መርሃ ግብሮች በድሬዳዋ እየተከበረ ነው

4ኛው ናፍቆት ድሬ አለም አቀፍ የድሬዳዋ ቀን በሚል ስያሜ ከዛሬው የመክፈቻ የእግር ጉዞ የብሄር ሄረሰቦች ባህል፣ ታሪክ፣ ቋንቋና የማንነት መገለጫዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ ሲንፖዚየም፣ የስነ-ፅሑፍ ስራዎች፣ስፖርታዊ ውድድሮች የልማት ፕሮጀክቶች ጉብኝት እንዲሁም አብሮነትን በሚያጠናክሩ ሁነቶች ለቀጣይ 5 ቀናት ይከበራል። ናፍቆት ድሬ የድሬዳዋ ተወላጆች እና ወዳጆችን ከመላው ዓለም በሰባሰብ ናፍቆታቸውን ወዳጅነታቸውን የሚያጠናክሩበት ከመሆኑም ባለፈ በአስተዳደሩ በማህበራዊ እና…

Read More

ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በ3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ተሸላሚ ሆነ

ተቋሙ በፎረሙ ለአነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች ባበረከተው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ተሸላሚ ሆኗል፡፡ 3ኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ላይ የተሳተፈው ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ በመንግስት ከተቋቋሙ የአነስተኛ ብድር እና ቁጠባ ተቋማት መካከል ለአነስተኛ እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የላቀ የብድር፣ የቁጠባ እና የሙያ ድጋፍ በመስጠት ሶስተኛ ደረጃ በመውጣት የክሪስታል እና ሰርተፍኬት ተሸላሚ ሆኗል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ምክትል ጠቅላይ…

Read More