በአስተዳደሩ ለ19ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ ተገለጸ
በድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት፣ ኢኮኖሚ ንግድና ኢንድስትሪ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮን የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ውይይት አካሂዷል። በሪፖርቱም በበጀት አመቱ በከተማ እና በገጠር የስራ እድል ፈጠራ በግብርና በማህበራዊ እና በአገልግሎት ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ መመዝገቡ ተገልጿል። በበጀት አመቱ ለ19 ሺ ዜጎች የስራ እድል መፈጠሩ የተገለጸ…


