በድሬዳዋ አስተዳደር የተከሰተውን የሲሚንቶ እጥረት ችግር ለመፍታት በመሰራት ላይ እንደሚገኝ የአስተዳደሩ ንግድ ፅህፈት ቤት አስታወቀ ።
በድሬዳዋ አስተዳደር ላይ በየቀኑ ሲሚንቶ የሚያመርቱ ሁለት ግዙፍ ፋብሪካዎች ያሉ ሲሆን እነዚህም የናሽናል ሲሚንት አክሲዮን ማህበርና ፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው ። እነዚህ የሲሚንቶ ፋብሪካዎች በየቀኑ በርካታ ሲሚንቶዎችን እያመረቱ ቢሆንም ነገር ግን በከተማዋ ላይ በሚፈለገው መጠን የሲሚንቶ አቅርቦት ባለመኖሩ ምክንያት በድሬዳዋ አስተዳደር ላይ ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ እጥረት እየተስተዋለ ይገኛል ። ይህንንም በማስመልከት የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ፅህፈት…


