ከነውጠኛው ህወሓት ጋር የሽብር ተግባር ለመፈፀም እየተንቀሳቀሱ መሆኑን የተጠረጠሩ 18 ሰዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ::
በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሰጡት የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ኮምሽነር አለሙ መግራ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች ጋር 9 የተለያዪ ሽጉጦቸ ÷ጥይቶች÷ የተለያዪ የባንክ ደብተሮች ÷ፓስፖርቶች ÷ሰነዶች÷መአድኖችና ላፕቶፖች መያዛቸውን ገልፀዋል። ፖሊስ የህዝቡን ደህንነት የማስጠበቅ አንዲሁም የሽብርተኛውን ህወሓት የሽብር ተግባር ለማክሸፍ በንቃት እየሰራ እንደሚገኝ ኮምሽነር አለሙ መግራ ጨምረው ገልፀዋል።ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር የሚያደርገውን የተለመደ ትብብር መቀጠለም ይገባዋል ብለዋ።


