የድሬደዋ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ::
ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር አብይ አህመድ በ ተላለፈው ሀገር የማዳን የክተት ዘመቻ ለመከላከያ ሰራዊቱ ድጋፍ ለማድረግ የተቋሙ ሰራተኞች ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱም የተቋሙ አመራርና ባለሙያዎች በግንባር ዘምቶ ህይወቱን ለሚሰዋው የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ከጎናቸው ነን በማለት ከደሞዛቸው ለመደገፍ መስማማታቸውን የተቋሙ ሰራተኞች ገልፀዋል፡፡


