በአስተዳደሩ በፍትህ ዘርፍ የተዘገቡ ውጤቶችን ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለፀ::

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ.ፍትህ ሚኒስቴር የፍትህ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ተስፋዬ ዳባ የተመራ ልዑክ የድሬደዋ አስተዳደር ፍትህ ፀጥታና ህግ ጉዳዮች ቢሮ የሶስት ዓመት የፍትህ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን እቅድ የገመገመ ሲሆን 2018 ዓ.ም የፍትህ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን እቅድ የመጀመሪያ ግማሽ አመት የስራ እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሀር በአስተዳደሩ በተለይ ባለፉት ሶስት አመት…

Read More

የአሜሪካ ኤምባሲ ልዑክ እና የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርትን ለማጠናከር በጋራ ለመስራት ተወያዩ::

የአሜሪካ ኤምባሲ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ጽሕፈት ቤት ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ ከተማ በመገኘት የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት አሰጣጥን ለማሻሻል ያለመ ውይይት ከአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ጋር ውይይት አካሄደ። በምስራቅ አፍሪካ የቀጣናው የእንግሊዝኛ ቋንቋ ኃላፊ የሆኑት ሚስተር ጆርጅ ኤም ቺነሪ የተመራው የልዑካን ቡድን ከቢሮው ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅት በዋናነት…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር ባለፉት 6 ወራት በህገ-ወጥ መልኩ ሊወጡና ሊገቡ የነበሩ ከ 1.7 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ምርቶች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ::

በድሬዳዋ አስተዳደር የንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት (የ6 ወራት) የፀረ ኮንትሮባንድና ህገ-ወጥ ንግድ መከላከል፣ የኑሮ ውድነት መቀነስና ዋጋ ማረጋጋት እንዲሁም ኤክስፖርት ምርት ማሳደግ የጋራ ግብረ-ኃይል ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዛሬው ዕለት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በዚህም በመድረኩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ንግድ፣ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ ባለፉት 6 ወራት…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽንና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በዛሬው እለት በጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ የመስክ ምልከታውን አካሄደ።

ቋሚ ኮሚቴው በዛሬው እለት በአስተዳደሩ ስር ያሉ ሶስት የተለያዩ ቦታዎች ላይ ተገንብተው ለነዋሪው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የጋራ መኖሪያ ቤት ኮንዶሚኒየም ላይ የመስክ ምልከታውን ያደረገ ሲሆን በጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ላይ ያሉትን ማህበራቶች የስራ እንቅስቃሴያቸውን ተመልክተዋል። የዛሬ የመስክ ምልከታቸውን አስመልክተው አስተያየታቸውን የሰጡት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማ ልማት ኮንስትራክሽን እና ማዘጋጃ ቤታዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል። 1ኛ. ካቢኔው በቀዳሚነት የተወያየው የመንግስትና የግሉ ዘርፍ በአጋርነት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በጋራ ማከናወን እንዲችሉ የወጣው ደንብ ላይ ነው። በዚህም የግሉ ዘርፍ ለሀገራዊ እድገትና ልማት መሰረት በመሆኑ በአስተዳደሩ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች ላይ የግሉ ዘርፍ የበኩሉን ሚና መወጣት እንደሚገባው ካቢኔው የጠቆመ ሲሆን…

Read More

በወረዳ ሁለት (02) እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ለወረዳው በከፍተኛ ሁኔታ መነቃቃት እየፈጠረ እንደሚገኝ የወረዳው ነዋሪዎች ተናገሩ።

በድሬዳዋ በወረዳ ሁለት አስተዳደር በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተተገበረ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ፤ በመጀመሪያው ምዕራፍ ከአኪር ድልድይ(ከሰብሪያ ሪዞርት) እስከ ቻይና ድልድይ እንዲሁም ከብሪጅ ድልድይ እስከ ማደያ እና ከመስቀለኛ እስከ ሸረፍ ሆቴል ሰባተኛን አጠቃሎ ባሉት አካባቢዎች እየተሰራ ይገኛል። በዚህም የኮሪደር ልማቱ እየተከናወነባቸው የሚገኙ አካባቢዎች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች ልማቱ ለወረዳው በከፍተኛ ሁኔታ መነቃቃትን እየፈጠረ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ከዚህ ቀደም…

Read More

ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች ያሉ ማህበረሰቦችን ኑሮ የማሻሻል ድጋፍ እንደሚቀጥል ተገለፀ::

በድሬዳዋ የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን EAC ፕሮጀክት እየተደረጉ የሚኙ ድጋፎች የዜጎችን ማህበራዊ የኑሮ ዋስትና እንዲረጋገጥ እያገዘ መሆኑ ተገልጿል። ለአምስት አመት የሚቆየውና ሁለተኛ አመቱን የያዘው የማህበረሰብ አየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭነት መቋቋም ፕሮጀክት EAC እስካሁን በምግብ ማብሰል ንግድ ዘርፍ፣በባልትና ውጤቶች ንግድ ፣በሸቀጣሸቀጥ ንግድ፣በእንጀራ መጋገር ንግድ፣በብሎኬት ማምረት እና በተሽከርካሪዎች ማጠብ ስራ ዘርፍ ላይ መሰማራት ለሚፈልጉ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ…

Read More

የሚዲያና የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሮችን ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ::

በድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ እና የመረጃ አካላትን የማብቃትና ማፍራት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አቤል ሞላ የተመራ ቡድን በወረዳ 01፣02፣06፣08፣እና 09 የድጋፍ እና ሱፐርቪዥን ስራው ከናውኗል። በ2018 ዓ.ም ግማሽ አመት የወረዳ የኮሚኒኬሽን ዘርፍ ለማጠናከርና የአገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ የሙያዊ ድጋፍና ክትትል በዛሬው ዕለት አካሂዷል። በክትትልና ድጋፉ አቶ ብሩክ ወርቅነህ እንደገለፁት በአስተዳደሩ እየተከናወኑ…

Read More

በከተማዋ እየተመዘገበ ለሚገኛው ሁለንተናዊ ልማት እና ሰላም የአመራሩ እና የህዝቡ ለአንድ አላማ ተባብረው የመስራታቸው ውጤት እንደሆነ ተገለፀ።

ይህንን የአስተዳደሩን እድገት እና ሰላም ለማደፍረስ ህዝቡን እና አመራሩን ሆድ እና ጀርባ ለማድረግ የሚጥሩ አካላትን ማውገዝ እንደሚገባ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የኦሮሚኛ ቋንቋ የኪነጥበብ ተፅዕኖ ፈጣሪ አርቲስት መሀመድ ቆጴ ተናግሯል። የ1960 የኦሮሚኛ ቋንቋ የኪነጥበብ መነቃቃት ውስጥ ጉልህ አሻራ ከነበራቸው የዘርፉ አርቲስቶች መሀል የግጥም እና ዜማ ደራሲው መሀመድ አህመድ ሙሳ ወይም በቅፅል ስሙ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወረዳ 8 የዕቅድ አፈጻጸምን ገመገመ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት የህግ፣ ፍትህና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወረዳ 8 የዕቅድ አፈጻጸማቸውን የገመገመ ሲሆን በልማት፣ በመልካም አስተዳደር ከነዋሪው ጋር የተቀናጀ የሰላም አደረጃጀት በመፍጠር በተለይ በፀጥታ ዘርፍ ላይ ውጤታማ ስራ መስራት መቻሉን የወረዳ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አብዱላዚዝ አሜ ለቋሚ ኮሚቴ አብራርተዋል፡፡ በተከበሩ አቶ አህመድ አብደላ ሰብሳቢነት የሚመራው የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት…

Read More