ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ

********************** ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በባሌ ዞን፣ ደሎ መና ወረዳ በመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመረውን የወልመል ወንዝ መስኖ ልማት ፕሮጀክትን መርቀዋል። ፕሮጀክቱ የወልመል ወንዝን በመስኖ በሚገባ በመጠቀም የግብርና ምርታማነትን በማላቅ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተከናወነ መሆኑም ተገልጿል። ፕሮጀክቱ ዘላቂ የገጸምድር የመስኖ ሥርዓት በመገንባት፤ የግብርና ሥራው ለዘመናት በዝናብ ውኃ ላይ ተመስርቶ የነበረውን የአካባቢውን ሕዝብ…

Read More

የድሬዳዋ ስታድየም አለም አቀፍ ጨዋታዎችን የማስተናገድ አቅሙን ለመገምገም የካፍ ከፍተኛ ባለሙያ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ላይሰንሲንግ ዳይሬክተር የተመራ ልዑክ ቡድን ጉብኝት አድርገዋል

የካፍ ልዑክ ቡድኑ በመጀመሪያ የድሬዳዋ ስታድየም አጠቃላይ ምልከታ ያደረጉ ሲሆን በተጨማሪም የድሬዳዋ ሆቴሎች እና ሆስፒታሎችን ተዟዙረው ተመልክቷል ። የድሬዳዋ ስታዲየም ገምጋሚ ልዑካን ቡድኑ በካፍ ኢንስፔክሽን ቢያንካ ብሬንዳ ሲመራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ላይሰንሲንግ ዳይሬክተር አቶ አመሀ ተስፋዬ ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ካሊድ መሐመድ ናቸው። የድሬዳዋ አስተዳደር ስፖርት ኮሚሽን የድሬዳዋ ስታዲየምን የካፍን መስፈርት ለማሟላት…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት፡-

******************** የባሌ ዞን የመጀመሪያ ቀን ጉብኝት ያሳየን በድንቅ ተፈጥሮ እና በልማት ሥራ እድገት መካከል ያለውን መስተጋብር ነው። በአስደናቂ ብዝኅ መልኩ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የቱሪዝማችን አንዱ የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ ቀጥሏል። ይኽ እምቅ አቅም በፓርኩ እምብርት ላይ የተገነባው የዲንሾ ሎጅ በቅርቡ ሲጠናቀቅ የበለጠ ይጠናከራል። በአቅራቢያው በመገንባት ላይ ያለውና በቅርቡ የሚጠናቀቀው የሶፍኡመር ሎጅ ቱሪዝምን የኢኮኖሚያችን ቁልፍ መሪ…

Read More

በፈረንሳይ ለቡግ (Le Bugue) ከተማ ከንቲባ የተመራ ልዑካን ቡድን የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በማከናወን በድሬዳዋ የነበረውን ቆይታ አጠናቀቀ

ልኡክ ቡድኑ ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ጋር በጋራ በመሆን በክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ፓርክ አረንጓዴ አሻራውን በማሳረፍ በድሬዳዋ የነበረውን የልምድ ልውውጥ አጠናቋል። በዚህም የፈረንሳይ ለቡግ (Le Bugue) ከተማ ከንቲባ ሊዮኒዳስ ሰርጅ ችግኝ መትከል አካባቢያችንን ለመጠበቅ እንዲሁም ነፋሻማ አየር ለማግኘት ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳለው ገልፀዋል። ከንቲባው አያይዘውም ድሬዳዋ ለአረንጓዴ አሻራ ከፍተኛ ትኩረት…

Read More

በፈረንሳይ ሌጉ ከተማ ከንቲባ ሊዮኒዳስ ሰርጅ የተመራ 11 አባላትን የያዘ ልዑካን ቡድን ከሦስት ቀን በፊት ድሬዳዋ እና የሌጉ ከተማን እህትማማችነት ለማጠናከር ድሬዳዋ መግባታቸው ይታወሳል

ድሬዳዋ እና የፈረንሳይዋ ሌጉ ከተማ እህትማማች ከተሞች ሲሆኑ በትምህርት፣ በጤና እና በሌሎችም ማህበራዊ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርመዋል። በፈረንሳይ ለቡግ (Le Bugue) ከተማ ከንቲባ የተመራ ልዑካን ቡድን ዛሬ ማምሻውን ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን የድሬዳዋ-የኮሪደር ልማት ጎብኝተዋል ። ሉኡካን ቡድኑም ድሬዳዋ በኮሬደር ልማት ሥራን በማስፋፋት ረገድ አስገራሚ ተግባራትን እየሰራች እንደምትገኝ የፈረንሳይዋ የሉቡግ ከተማ ከንቲባ ሰርጅ…

Read More

“በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የማህበረሰቡን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ ናቸው” -ኮማንደር ምትኩ ዳባ

የፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ምስራቅ መምሪያ አመራሮች በአጠቃላይ በቀጠናው ሰላም እና ፀጥታ ዙሪያ በድሬዳዋ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፤ ከውይይቱ ጎን ለጎን በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በዚህም በጉብኝቱ ወቅት ያነጋገርናቸው የምስራቅ ፈጥኖ ደራሽ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ምትኩ ዳባ በቀጠናው ዙሪያ ውይይት ከመደረጉ ጎን ለጎን በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን በተጨባጭ…

Read More

የእርስ በርስ መደጋገፍና መረዳዳት ባህል በማጠናከር የአቅመ ደካማ ቤተሰቦችን ህይወት በላቀ ደረጃ መለወጡ ይጠናከራል

ባለፉት ሰባት አመታት መንግስት የዜጎች ሁለንተናዊ ብልፅግናን እንዲረጋገጥ እያከናወነ በሚገኘው ስራ አበረታች ለውጥ እየተገኘ ነው። የፌደራል ተቋማት አደረጃጀት የኢኮኖሚ ክላስተር የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ወረዳ ስር የሚገኙ አራት የመንግስት የልማት ድርጅቶች በክረምት በጎ ፈቃድ በድሬደዋ ለአቅመ ደካማ ቢተሰቦች ያስገነቧቸውን 20 ቤቶች ዛሬ መርቀው አስረክበዋል ። የድሬደዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በክላስተሩ ስር የሚገኙ የፌደራል ተቋማት በድሬደዋ…

Read More

ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ በባለፉት ሦስት ወራት ከ301 ሚሊዮን ብር በላይ ለደንበኞቹ የብድር አገልግሎት መሰጠት መቻሉን ገለጸ

ድሬ ማይክሮ ፋይናንስ የ2018 የ1ኛ ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ በዛሬው እለት አካሂዷል በግምገማ መድረኩም የቅርንጫፎችና የዋናው መሥሪያ ቤት የ1ኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎባቸዋል። በመድረኩም በተቋሙ በባለፉት ሦስት ወራት በብድር ስርጭት ረገድ 324 ሚሊዮን ብር ብድር ለማሰራጨት ታቅዶ 301 ሚሊዮን ብር ለደንበኞቹ የብድር አገልግሎት መስጠት የተቻለ ሲሆን ይህም የእቅድን…

Read More

በትምህርት እና በስፖርቱ ዘርፍ ድሬዳዋን እና የፈረንሳይዋ ለቡግ (Le Bugue) ከተማን የማስተሳሰር ስራ በተጠናከረ መልኩ እንደሚሰራ ተገለፀ::

በፈረንሳይ ለቡግ (Le Bugue) ከተማ ከንቲባ የተመራ ልዑካን ቡድን የኖትሮዳም፣ የማሪያም ሰፈር እና የለገሀሬ ት/ቤትን በመጎብኘት ለተማሪዎች የፈረንሳይን ባህላዊ ስፖርት ራግቢን አስተዋውቀዋል፤ ለስፖርቱ የሚውሉ ቁሳቁሶችንም አበርክተዋል። በዚህም በጉብኝቱ ወቅት ያነጋገርናቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ ጉብኝቱ በድሬዳዋ የሚገኙ ት/ቤቶችን በፈረንሳይ ከሚገኙ ት/ቤቶች ጋር ለማስተሳሰር እና ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳለው ተናግረዋል። አቶ…

Read More

በፈረንሳይ ሌጉ ከተማ ከንቲባ የተመራ ልዑካን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎበኘ

ልዑኩ በጉብኝቱ የድሬዳዋን ነፃ የንግድ ቀጠናን፣ ደረቅ ወደብን፣ አዲሱ ምድር ባቡርን እንዲሁም የድሬዳዋ ኮንቬንሽን ማዕከልን እና የድሬዳዋ አለም አቀፍ እስታድየምን ተመልክቷል። የፈረንሳይዋ ሌጉ ከተማ ከንቲባ ሊዮኒዳስ ሰርጅ በድሬዳዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የከተማዋን እድገት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያፋጥን ገልፀው፤ የጉብኝቱ ዋንኛ ዓላማም የልምድ ልውውጥ ለማረግ እንዲሁም በቀጣይ በጋራ ለመስራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ለመመልከት መሆኑን አብራርተዋል። ከንቲባው አያይዘውም…

Read More