የሀገራችንን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን እንዲሁም ጠንካራ ኢኮኖሚን ለመገንባትና የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የዲጂታል አሰራሮችን ማጎልበት እንደሚገባ ተጠቆመ::

የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር እና የካቢኔ አባላት በፕላንና ልማት ሚኒስተር ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ (ዶ/ር) ከተመራ ልዑካን ቡድን ጋር በፌደራል ደረጃ ተተግብረው ውጤታማ የሆኑ ዲጂታላይዝ አሰራሮችን እና ተሞክሮዎችን ወደ አስተዳደሩ ለማውረድ በሚቻልባቸው ነጥቦች ላይ ውይይት አድርገዋል። በዚህም በውይይት መድረኩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በፌደራል ደረጃ የተገኙ ተሞክሮዎችን ወደ ድሬዳዋ አስተዳደር ለማስፋት አስተዳደሩ…

Read More

የድሬዳዋ አስተዳደር ከተማ ስፖርት ክለብ ከታን ኢንጂ ነሪንግ እና ትሬዲንግ ጋር ለ 3 አመት የሚቆይ የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራርሟል::

በፊርማ ስነ-ስረአቱ ላይ የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋችና የታን ኢንጂነሪግ እና ትሬዲንግ ስራ አስኪሀጅ አቶ ስፉአድ ኢብራሂም ድሬዳዋ ተወልጄ ያደኩበት እንደመሆኑ የድሬደዋ እግርኳስ ስፖርት ክለብን በዚህ መልኩ በስፖንሰር ሺፕ ድጋፍ ለማድረግ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል ሲል ገለጿል። ክለቡ በእግርኳስ መድረክ ጠንካራ ተፎካካሪ እንዲሆን ቀጣይነት ያለው ሌሎች ድጋፍችንም ለማድረግ ድርጅታቸው ዝግጁ መሆኑን አመላክተዋል። የድሬዳዋ ከተማ ስራ አስኪያጅና…

Read More

ለእመርታ ቤተ መፅሀፍ ግብአት ማሰባሰቢያ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ::

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በተፃፈው በመደመር ትውልድ መፅሀፍ ሽያጭ እንዲሁም በአስተዳደሩ ድጋፍ ዘመናዊና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለተገነባው እመርታ ቤተ-መፅሀፍ ግብአት ማሰባሰቢያ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ተወካይ እና የከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን ሁሉም ተቋማት እንዲሁም በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የሚገኙ የድሬዳዋ ወዳጆችና ደጋፊዎች ለቤተ-መፅሀፉ…

Read More

የሚዲያ አጠቃቀምን በማዘመን ገዢ ትርክትን ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት በየደረጃው ያለው አመራርና አባል ሚና ወሳኝ ነዉ ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ ድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ኢፍቱ መሀመድ ገለፁ

በብልጽግና ፓርቲ ድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ከሴቶች ክንፍ ከተቋማት ና ከወረዳዎች ለተውጣጡ ለግንባር ቀደም አመራር እና አባላት በሚዲያ አጠቃቀም ላይ ያተኮረ ስልጠና ሰጥቷ። በመድረኩም በብልጽግና ፓርቲ ድ/ዳ/ቅ/ጽ/ቤት የሴቶች ክንፍ ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ኢፍቱ መሀመድ በንግግራቸው የሚዲያ አጠቃቀምን በማዘመን በእውነት እና በእውቀት ላይ የተመሰረተ የሚዲያ እና የተግባቦት ተግባራትን ለመፍጠር በየደረጃው ያለው አመራር ሚና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።…

Read More

የወረዳ አመራሮች ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ህገ-ወጥ የውሃ አጠቃቀምን መከላከል ላይ አተኩረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ::

በዛሬው ዕለት የድሬዳዋ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን የ2017 ዓ.ም እቅድ ክንውን እና 2018 ዓ.ም መሪ እቅድ ላይ ከድሬዳዋ አስተዳደር የከተማ ወረዳዎች አመራሮች ጋር እንዲሁም ከከተማ አጎራባች ገጠር ቀበሌ አመራሮች ጋር ተወያይቷል። የመልካ ቁጥር ሁለት የንፁህ መጠጥ ውሃ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ላይ ከተደረገ የመስክ ምልከታ በማስቀጠል ሰፊ የመድረክ ውይይት የተደረገ ሲሆን የባለ ስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር…

Read More

አንድ ሙያ ለአንድ ዜጋ በሚል መርሃግብር የክረምት የሙያ ክህሎት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ ከ250 በላይ ወጣቶች ተመረቁ::

በድሬደዋ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ዜጎች ቢያንሰ የአንድ ክህሎት ባለቤት እንዲሆኑ ለማድረግ “አንድ ሞያ ለአንድ ዜጋ” በሚል መሪ ቃል የወጣቶች የክረምት ስልጠናን ሲከታተሉ የነበሩ 270 ወጣቶችን አስመርቋል። በኹነቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ያለፉትን 3 ወራት በ14 ዘርፎች የተሰጠውን ክህሎት መር ሰልጠና የእረፍት ጊዜያቸውን በመሰዋት ወስደው የተመረቁት ወጣቶቹ ህብረተሰቡ ለዘርፉ ያለውን የተዛባ አመለካከት…

Read More

መምህራን ለትዉልድ ቀረፃና ለሀገር ግንባታ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው ተገለፀ::

የድሬዳዋ መምህራን ማህበር የ2ኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና የ 37ኛው መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ ማካሄድ ጀምሯል። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የኢትዮጲያ መምህራን ማህበር ተወካይ ወ/ሮ ደብሪቱ ጌታቸው ማህበሩ የመምህራንን መብትና የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ ባለፈ በሀገራዊ ነባራዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የማህበሩ አባላት ቁጥር በየጊዜው እየጨመረ እንደሚገኝ የገለፁት ወ/ሮ ደብሪቱ ማህበሩ የእርስ በእርስ ትስስርን የማስፋት ስራ…

Read More

ከ20 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነባው የሳቢያን ጠቅላላ ሆስፒታል የጽኑ እና የውስጥ ደዌ ህክምና ክፍል ተመረቀ::

በድሬዳዋ አስተዳደር በዛሬው እለት በይፋ የተመረቀው ደረጃውን የጠበቀ የጽኑ ህሙማን እና የውስጥ ደዌ ህክምና ክፍል የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ጥራት በማሳደግ ረገድ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ተገልጿል። በመርሃ ግብሩም ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክብር አቶ ከድር ጅሀር በዛሬው እለት የተመረቁ የህክምና መስጫ ክፍሎች እንደ ሀገር የተጀመረውን የጤና ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን እቅድ የሚያሳኩ መሆኑን ገልጸዋል። የሳቢያን ጠቅላላ ሆስፒታል…

Read More

ሰው ተኮር በሆኑ ተግባራት አቅመ ደካማ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን የማገዝ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ

የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮና ተጠሪ ተቋማት የክረምት በጎ-ፈቃድ አገልግሎት አካል በሆነው የአቅመ ደካሞች የቤት እድሳት በተለያዩ ወረዳዎች የአረጋውያን ቤቶችን እያስገነቡ ይገኛሉ በዛሬው ዕለትም በወረዳ አራት ሁለት የአቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታ አስጀምረዋል። በዚህም በመርሃ-ግብሩ የተገኙት የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር ከለውጡ ማግስት ጀምሮ በሰው ተኮር ተግባራት አቅመ…

Read More

አንድነትን ፍቅርን ይቅርታን እና አብሮነትን የሚያጎላው የመስቀል ደመራ በዓል በአስተዳደሩ በድምቀት ተከብሯል

በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በየዓመቱ መስከረም 16 ቀን የሚከበረው የደመራ በዓል በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ በለገሀር አደባባይ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ክዋኔዎች በድምቀት ተከብሯል፡፡ በበዓሉ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣የድሬዳዋ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች፣ቀሳውስትና ዲያቆናት፣ምዕመናንና ከተለያዩ አለማት የመጡ ቱሪስቶች ተሳትፈዉበታል። በበዓሉ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ተወካይና የከንቲባ ፅ/ቤት እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊው አቶ ገበየሁ ጥላሁን በመገኘት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን…

Read More