በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የከተማዋን የንግድ፣ የኢንደስትሪና የኢንቨስትመንት ማዕከልነት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያጠናክሩ መሆናቸው ተጠቆመ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ የተመራ ልኡካን ቡድን ከድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ እንዲሁም ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በድሬዳዋ አስተዳደር እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም የድሬዳዋ አስተዳደር ልዩ ኢኮኖሚክ ዞንን፣ አማ የምግብ ዘይት ፋብሪካን፣ የተለያዩ የብረታ ብረት ውጤቶችን የሚያመርተውን ድሬ ስቲል ፋብሪካን፣ ደረቅ ወደብን፣ በኢንደስትሪ መንደር…


