የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን፣ ለአንድ ሀገር ለማሰብ ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመደመር እሳቤ ዙሪያ አራተኛ መጽሐፋቸውን አስመርቀዋል። የመደመር መንግሥት የተሰኘው መጽሐፋቸው በቀደሙት የመደመር መፃሕፍት የተቀመጡ ነጥቦች ወደ መንግሥታዊ ወይም ተቋማዊ ፍኖት የሚመጡበትን ዓውድ የሚያትት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ፥ ኢትዮጵያ ለሁላችንም ትበቃለች፤ የምንደመረው በአንድ ጭንቅላት ለማሰብ ሳይሆን ለአንድ ሀገር ለማሰብ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የአቅም እና የአቋም ድምር…


