በትንሿ ኢትዮጵያ፣ በበረሀዋ ገነት፣ በጉራማይሌዋ የፍቅር ከተማ ድሬ ገብተናል፡፡

በድሬዳዋ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበል ላደረጉልን ለድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ፣ ለከተማዋ ከፍተኛ አመራሮች፣ ለሀገር ሽማግሌዎች እና ለከተማው ህዝብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ፡፡ በቆይታችን የኮሪደር ልማት ስራዎችን ጨምሮ በከተማዋ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን የስራ ሂደት የምንመለከት ይሆናል፡፡

Read More

የኑሮ ውድነቱን እና የዋጋ ግሽበቱን ለማረጋጋት ‘የኢትዮጵያን ይግዙ’ የንግድ ሳምንት ከፍተኛ አስተዋፆ እንዳለው ተገለፀ

በድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ የተዘጋጀው ሁለተኛው “የኢትዮጲያን ይግዙ” የንግድ ሳምንትን በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ ተከፍቷል። የንግድ ሳምንቱ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ እንደሚካሄድ የገለፁት የድሬዳዋ አስተዳደር ንግድ ኢንደስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዲ ሙክታር ለአምስት ተከታታይ ቀናት ማለትም ከነሀሴ 12 እስከ ነሀሴ 16/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ አመላክተዋል።…

Read More

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ::

ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡ በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡ በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው…

Read More

ፈናን ፔይ ሻምፒዮና የታዳጊ ወጣቶች የብስክሌት ውድድር ተጠናቀቀ

ታዳጊ ኢሳኮር ፍሬው የውድድሩ አሸናፊ በመሆን በአንደኝነት አጠናቋል። “በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳጅ የሆኑና በሀገራችን የማይዘወተሩ አዳዲስ የብስክሌት ውድድር ዓይነቶችን በማስታዋወቅ ታዳጊ ወጣቶችን አቅምና ችሎታ አዳብረን ሀገራቸውን የሚወክሉ ውጤታማ ስፖሮተኞችን የማፍራት እቅዳችን ውጤት ማሳየት ጀምሯል ” ብለዋል፤ የፈናን ፔይ ሻምፒዮና የታዳጊ ወጣቶች የብስክሌት ውድድር አዘጋጅ አቶ ቢኒያም ነገሱ ። “ድሬዳዋን የብስክሌት ከተማ ማድረግ ” ግቤ ፣…

Read More

“ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ሀሳብ የብልፅግና ፓርቲ ያለፉት ዓመታት ጉዞና የቀጣይ ዓመታት የትኩረት መስኮች ላይ የሚመክር መድረክ በድሬዳዋ በትላንትናው እለት መካሄድ ጀመረ።

በብልፅግና ፓርቲ ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለአስተዳደሩ አጠቃላይ አመራሮች የተዘጋጀው የምክክር መድረክ ቃል በተግባር የተገለጠበት የፓርቲው ያለፉት ዓመታት ጉዞ እንዲሁም በቀጣይ ስኬቶችን ለማስቀጠል፣ ክፍተቶችን ለመሙላትና በእቅድ የተያዙ ስራዎችን የሕዝቡን የላቀ ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ በውጤታማነት መፈፀም የሚያስችል አቅም መፍጠሪያ መድረክ ነው። መድረኩ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።

Read More

በኢትዮጵያ የብስክሌት ስፖርት ውድድር ታሪክ ውስጥ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የጥሎ ማለፍ የታዳጊዎች ውድድር በድሬዳዋ ተከናወነ

የፈናን ፔይ የብስክሌት ሻምፒዮና የጥሎ ማለፍ ጫወታ አንደኛና ሁለተኛ ሆነው ባጠናቀቁት በአቤኔዘር አለሙና እና ኢሳኮር ፍሬው መካከል የታየው ፉክክር በስፍራው ከታደመው የስፖርት አፍቃሪ እና ተመልካች ከፍተኛ አድናቆት ተችሮታል። አርባ ሁለት ዙሮችን በሚሸፍነውና በያንዳንዱ ዙር መጨረሻ የሆነ ተወዳዳሪ ከጫወታ ውጪ እየሆነ የመጨረሻዎቹ ሁለት ተወዳዳሪዎች እስኪቀሩ ድረስ ጠንካራ ፣ አጓጊና ብርቱ ፉክክር በታየበት በዚህ በአራተኛው ቀን የፈናን…

Read More

የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በክረምት የበጎ ፍቃድ መርሃ-ግብር በድሬዳዋ በአሰሊሶ ክላስተር በሚገኙ ሁለት የገጠር ቀበሌዎች የአረጋውያን የቤት ግንባታን አስጀመረ

በዚህም የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሀ ይታገሱ በአሰሊሶ ክላስተር ገደንሰር ገጠር ቀበሌ እንዲሁም በአሰሊሶ ገጠር ቀበሌ የአቅመ ደካሞች የቤት ግንባታን አስጀምረዋል። የኢንደስትሪ ፖርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ፍስሀ ይታገሱ በክረምት የበጎ ፍቃድ ስራዎች አቅመ ደካማ ወገኖችን የማገዝ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፤ቤቶቹ በ 2 ሚሊየን ብር ወጪ እንደሚገነቡ እና በአንድ…

Read More

ፓስተር ዮሀንስ ኦላና እና ቤተሰቦቹ ከድሬዳዋ አስተዳደር እና ከዲያስፖራ ማህበር ጋር በመተባበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ

ፓስተር ዮሀንስ ኦላና እና ቤተሰቦቹ የምስራቅ መካከለኛው አፍሪካ ከሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት ቤተክርስቲያን ዋና የፋይናስ አስተዳዳሪ( CFO) ከድሬዳዋ አስተዳደር እና ከዲያስፖራ ማህበር ጋር በመተባበር የገጠር ሴት ተማሪዎች ሆስቴል ትምህርት ቤት ቅጥር ጊቢ ውስጥ ችግኝ ተክለዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ዳያስፖራ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ቢኒያም ግርማ እንደተናገሩት መንግስት የአየር ንብረት…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር በአረንጓዴ አሻራ ስራዎች ከሚተከሉት ችግኞች መካከል 85 በመቶ የሚሆኑት ለምግብነት የሚውሉ ፣ ሙቀት የሚቋቋሙ እና የውሃ እጥረት የሚችሉ ናቸው”። ወ/ሮ ፈቲህያ አደን – የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ

“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የድሬዳዋ እንደራሴዎች እና በስሩ ካሉ ተጠሪ ተቋማቶች ጋር በጋራ በመሆን የክረምት የበጎ ስራ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብርን አከናወኗል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን በመርሃግብሩ ላይ እንደተናገሩት ድሬዳዋ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላት ፣ ከፍተኛ የጎርፍ ተጋላጭነት እና…

Read More

/የንግድ ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ

የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ተገመገመ የድሬዳዋ አስተዳደር ም/ቤት የበጀት ኢኮኖሚ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የንግድ ኢንደስትሪ እና ኢንቨስትመንት ቢሮን የ2018 በጀት አመት እቅድ ገምግሟል። በዚህም የቢሮው የ2018 በጀት አመት እቅድ ቀርቦ የተገመገመ ሲሆን ከቋሚ ኮሚቴ አባላቶች ለተነሱ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ላይ የቢሮው አመራሮች ማብራሪያ ሰተዋል። ቢሮው የ2017 በጀት አመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ወቅት በውሰንነት የተለዩ እና…

Read More