በሀሪፍ ድሬና የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በድሬዳዋ ከተማ ከታህሳስ 26- ጥር 4 በሚደረገው ሀሪፍ ድሬ ሀገር አቀፍ የ2017 የብስክሌት ውድድር የወለወዋሎ አዲግራት አዲስ መድሃኒት ፋብሪካ ክለብ ብስክሌተኞች በግልና በቡድን የበላይነትን በመያዝ የመጀመሪያውን ቀን ውድድር አጠናቅቀዋል ፡፡
የመክፈቻ ውድድሩ በማውንቴን ብስክሌት ታዳጊ የፕሮጄክት ተወዳዳሪዎች 15.4 ኪ/ሜትር በሚሸፍን የ7 ዙር ውድድር የተጀመረ ሲሆን ይሳኮር ፍሬው፣ አቤኔዘር አለሙ እና ምህረት ሞገስ ከአንድ እስከ ሶስት በመውጣት ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል፡፡ በሰላሳ ስድስት ዙሮች 79.2 ኪ/ሜትር በሚሸፍነው ውድድር በቅርቡ የተመሰረተው ቶቶ ብስክሌት ክለብን ጨምሮ፣ ድሬዳዋ ከነማ፣ ድሬዳዋ ፖሊስ፣ ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፣ አዲስ አበባ እና የትግራዮ ወልዋሎ አዲግራት…


