ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1 ሺህ 500ኛው የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡- እንኳን ለ1 ሺህ 500ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ፡፡ የታላላቆቻችንን በዓል የምናከብረው የእነርሱን አርአያ ለመከተል ምክንያት እንዲሆነን ነው፡፡ ምን እንደሠሩ? ምን እንዳስተማሩ? ምን እንደገጠማቸው? ፈተናዎችን እንዴት እንዳለፉ? ታሪካቸውን እያነሣን እንማርበታለን፡፡ የመውሊድንም በዓል ስናከብር የነቢዩ መሐመድን(ሰዐወ) ፈለግ…


