ህብረተሰቡ የኮቪድ – 19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባቶችን በተመለከተ በተሳሳቱ መረጃዎች ሳይዘናጋ የመከላከያ ክትባቶችን ሊወስድ እንደሚገባ ተጠቆመ፡፡
የኮቪድ – 19 ወረርሽኝ መከላከያ ክትባት ዘመቻ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር፤ ከፍተኛ አመራሮችና የሃይማት አባቶች በተገኙበት በከንቲባ ፅ/ቤት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በይፋ ተጀምሯል፡፡ በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ከንቲባ ከድር ጁሃር በአስተዳደራችን ባሉት 10 የኮቪድ – 19 ወረርሽኝ መከላከያ የክትባት ዘመቻ ቀናት ከ60 ሺ በላይ ሰዎችን ለመከተብ ዕቅድ መያዙንና ዝግጅቶች ተጠናቀው ወደ ሥራ…


