“የጤናው ዘርፍ አርበኝነት ለሀገር ዕድገት!” በሚል መሪ ቃል ከጤና ባለሞያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ።

ውይይቱ በአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ስር ካሉ ጤና ተቋማት የተውጣጡ የጤና ባለሞያዎችና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች እንዲሁም ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ ማስተማሪያ ሪፈራል ሆስፒታል የጤና ባለሞያዎች ጋር የተደረገ ሲሆን ይሄንኑ ውይይት በአራት የመወያያ ማዕከላት በቀረበው “የጤናው ዘርፍ አርበኝነት ለሀገር ዕድገት!” በሚል መሪ ቃል የቀረበውን ፅሁፍ መሰረት በማድረግ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮችና የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ አመራሮች ተሳታፊዎችን በየመወያያ ማዕከላቱ አወያይተዋል።…

Read More

በድሬዳዋ ከተማ ወረዳ 2 ስር በሚገኙ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በተከናወኑ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ስራዎች የሺሻ ማጨሻ እቃዎችና ለጥቁር ገበያ ሊቀርብ የነበረ ህገ-ወጥ ነዳጅ እንዲሁም ተጠርጣሪ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ገለፀ

ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን 7 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑንምና በቀጣይም በህገ-ወጥ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦችና ንግድ ቤቶች ላይ የሚደረገዉ ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል ። በድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የሳቢያን ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ዋ/ኢ/ር አንበሉ አየለ ለድሬ ፖሊስ ሚዲያ እንደገለፁት አስቀድሞ በተከናወነ መረጃ ማሰባሰብን ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማዎች መሰረት በማድረግ ግንቦት…

Read More

“የጤና ባለሞያው በበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ መርሀ ግብር ላይ መሳተፉ ለሌሎች የሀገሪቷ ክፍል ጤና ባለሞያዎችም መልካም ተሞክሮ የሚሆን ነው።” – አቶ ዩሱፍ ሰኢድ የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ

#DGC ግንቦት 04/2017 “በወሊድ ወቅት በሚከሰት የደም እጥረት ምክንያት የሚከሰትን የእናቶች ሞት ለመታደግ ደማችንን እንለግሳለን” በሚል መሪ ሀሳብ በድሬደዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ስር ያሉ የጤና ተቋማት ጤና ባለሞያዎች የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ መርሀ ግብር አካሄዱ። የጤና ባለሞያዎቹ በወሊድ ምክንያት በሚፈጠር የደም እጦትና ሌሎች አደጋዎች የአንዲትም እናት እንዲሁም ነዋሪው ለህልፈተ ህይወት እንዳይዳረግ ደማቸውን በመለገስ ወገናዊ ኃላፊነታቸውን…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር የዲጂታል መታወቂያ የምዝገባ ሂደት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው

በድሬዳዋ አስተዳደር የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በየተቋማት እየተካሄደ ሲገኝ፤ በዛሬው ዕለትም በሳቢያን የመጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ምዝገባው ተጀምሯል፡፡ በዚህም ምዝገባውን ያስጀመሩት የድሬዳዋ አስተዳደር ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ አብዱለዚዝ ሻፊ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ታማኝነትን የሚዘረጋ፣ የተቋማትን ሥራ የሚያቀናጅ፣ በግለሰቦች ደረጃም የራስን መብት የሚያስጠብቅ መሆኑን አመላክተዋል። አቶ አብዱለዚዝ አያይዘውም ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የሀገርን…

Read More

አፍታሜይራ ግሩፕ የ 20 \ 80 ቤቶችን ለመገንባት ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር ስምምነት ተፈራረመ

አፍታሜይራ ግሩፕ ኢምፖርት ኤክስፖርትን ጨምሮ የተለያዩ ድርጅቶችን የሚያስተዳድር ሲሆን በአዲስ አበባም የተለያዩ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየሰራ ይገኛል ። በድሬዳዋ አስተዳደርም የ 20 \ 80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችለውን ስምምነት በዛሬው እለት ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር ተፈራርሟል ። አፍታሜይራ ግሩፕ ድሬዳዋ ላይ የሚያስገነባቸው ቤቶች በመሀል ከተማዋ ላይ ከመሆኑም በላይ የቤት ባለቤት ለመሆን ቅድሚያ 20…

Read More

የድሬዳዋ ባህልና ታሪክ ላይ እንዲሁም የባቡር መስመሮቿ ላይ ያተኮሩ ሁለት ፊልሞች ለምርቃት በቁ

የጀርመን ባህል ተቋም (ጎተ) ኢንስቲትዩት ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር የተሰሩ በድሬዳዋ ባህል፣ ታሪክና የባቡር መስመሮቿ ላይ ያተኮሩ ሁለት ፊልሞች በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመረቁ። በዚህም ለምርቃት ከበቁት ፊልሞች መካከል የመጀመሪያው አጭር ፊልም skins የተሰኘ ሲሆን ሂናን መሰረት በማድረግ በድሬዳዋ ከተማ ከመሰራረት፣ የባቡር መስመሮቿ፣ በኪነ ህንፃዎቿ፣ በገበያዎቿ፣ በማህበረሰቡ አለባበስ እንዲሁም ሌሎት የአኗኗር ዘይብዎች ላይ የሚስተዋሉ የባህል ልውውጦች…

Read More

በድሬዳዋ አስተዳደር ወረዳ 02 ባርገሌ አካባቢ በህዝብ ተሳትፎ የሚሰራ የጠጠር መንገድ ስራ ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሄደ ።

በድሬዳዋ አስተዳደር የአካባቢ ልማትና ህብረተሰብ ተሳትፎ ኤጀንሲ እና በወረዳ 02 አስተዳደር ፅህፈት ቤት በጋራ በመሆን የባርገሌ አካባቢ በህዝብ ተሳትፎ የሚሰራ የጠጠር መንገድ ስራ ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሄደ ። የባርገሌ አካባቢ ህብረተሰብ የበርካታ አመት ጥያቄ የሆነዉ 1 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ከጎሮ ሀዲድ ሀና ግሮሰሪ እስከ ባርገሌ ታክሲ ማዞሪያ ያለዉ መንገድ እንዲሁም የዉሃ መዉረጃ ቦይ ዲች ስራ እዉን…

Read More

4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ

“ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል መሪ ሐሳብ ሲካሄድ የነበረው 4ኛው ዙር ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የማጠናቀቂያ መርሐ-ግብር ተካሂዷል፡፡ በውድድሩ 1ኛ የወጡ ተወዳዳሪዎች 500 ሺህ ብር፣ 2ኛ ለወጡ 400 ሺህ ብር እንዲሁም 3ኛ ለወጡ 300 ሺህ ብር ተሸልመዋል፡፡ ከድሬዳዋ አስተዳደርም በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ እና በተግባራዊ ጥናትና ምርምር አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኝ ተማሪዎች እና ኢንተርፕራይዞች ተሳታፊ ሆነዋል። በውድድሩም…

Read More

የካብኔ ውሳኔዋች

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ውሳኔዎችን አስተላልፏል የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዋች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል 1ኛ፦ካብኔው በመጀመሪያ አጀንዳው የ10 አመት(2025-2035 እ.እ.አ) ኢንዱስትሪ ሮድ ማኘ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል ። በውይይቱም ነባር ኢንዱስትሪዋች ከፍ ማድረግና በቁጥርም እንዲጨምሩ የማድረግ እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዋች እንዲገቡ ማድረግ። ከውጭ የሚገቡ ጥሬ ምርቶችን ምንዛሬ በመቀነስ ጥራት ያለው ምርት…

Read More

የድሬ ማይክሮ ፋይናንስ የገንደገራዳ ቅርንጫፍን በዛሬው እለት አስመረቀ

የድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ የፋይናንስ ውስንነት የገጠማቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ከማድረግ አንስቶ በድሬዳዋ አስተዳደር በከተማ ሆነ በገጠር እየሰጠ ካለው አገልግሎት በተጨማሪም በሀረር እና በጂጂጋ ቅርንጫፎቹን በመክፈት ዘመኑን የዋጀ ዲጂታል ፋይናንስን በመተግበር የፋይናንስ አገልግሎቱን ፈጣን ፣ ቀልጣፋ እንዲሁም ደንበኛ ተኮር በሆነ መልኩ እየሰጠም ይገኛል ። የድሬ ማይክሮ ፋይናንስ ቅርንጫፎቹን በማስፋት በዛሬው እለትም የገንደገራዳ ቅርንጫፍን…

Read More